Tuesday, 24 February 2015

የኬንያ ፖሊስ 101 ኢትዮጵያዉያንን አሠሩ

ናይሮቢ፤ የኬንያ ፖሊስ 101 ኢትዮጵያዉያንን ማሠሩ
የኬንያ ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ ወደደቡብ አፍሪቃ ሊጓዙ ነበር ያላቸዉን ከመቶ የሚበልጡ ኢትዮጵያዉያንን ትናንት ማምሻዉን ማሠሩን አሶሲየትድ ፕረስ ከናይሮቢ ዘገበ። የኬንያ ልዩ የወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ኖህ ካቱሞ ለዜና ወኪሉ ዛሬ እንደገለፁት የታሠሩት 101 ወንዶች ኢትዮጵያዉያንና እነሱን በኬንያ ድንበር በኩል ሊያሾልኩ በመሞከር የተጠረጠሩ ሶስት ኬንያዉያን ናቸዉ። ካቶሙ እንዳሉት ኢትዮጵያዉያኑ ወደደቡብ አፍሪቃ ጉዟቸዉን ከመቀጠላቸዉ በፊት በቡድን በቡድን ሆነዉ ኬንያ መዲና ናይሮቢ በሚገኝ አንድ ቤት ዉስጥ አርፈዉ ነበር። ታሳሪዎቹ ዳኛ ፊት ቢቀርቡም እንግሊዝኛ ስለማይረዱና በአማርኛም የሚያስተረጉምላቸዉ ባለመገኘቱ ምክንያት ለጊዜ ክስ አልተመሠረተባቸዉም። እንደዘገባዉ ዳኛዉ ቪክቶር ዋኩሜሌ አስተርጓሚ እስኪገኝ ጉዳዩን ለነገ ቀጥረዋል። ከዚህ ቀደምም ለተመሳሳይ ጉዞ የተዘጋጁ 95 ኢትዮጵዉያን በኬንያና ታንዛንያ ድንበር አቅራቢያ መታሠራቸዉ ተዘግቧል። የኬንያ ፖሊስ ከአፍሪቃ ቀንዷ ሀገር ሰዎችን የሚያሸጋግሩት ወገኖች ኢትዮጵያዉያኑን በሕገ ወጥ መንገድ የሚያዘዋዉሩት የጦር መሣሪያ፣ አደንዛዥ እፆች፣ የዝሆን ጥርስና የመሳሰሉትን ነገሮች አስርገዉ በሚያስገቡበትና በሚያወጡበት መስመር እንደሆነ ገልጿል። ...... source.-www.dw.amharic

No comments:

Post a Comment