Tuesday, 3 February 2015
35 ሰዎች ቀይ ባህር ውስጥ ጠፉ * የ9 ኢትዮጵያውያንን ሰውነት አግኝተዋል
35 ሰዎች ቀይ ባህር ውስጥ ጠፉ * የየመን ነብስ አድን ሰራተኞች የ9 ኢትዮጵያውያንን ሰውነት አግኝተዋል
ዘ-ሐበሻ) ዜግነታቸው ከኢትዮጵያ ሶማሊያና አካባቢው ሃገራት እንደሆነ የሚገመት 35 አፍሪካውያን ቀይ ባህር ውስጥ ይጓዙበት የነበረችው ትንሽዬ ጀልባ ሰጥማ የት እንደደረሱ ሊታወቅ አለመቻሉን የየመን ባለስልጣናት አስታወቁ::
በደቡባማው የየመን ክፍል ቲያዝ አቅራቢያ በሚገኘው የቀይባህር ውስጥ ሰጥመዋል ስለተባሉት አፍሪካውያን የየመኑ ባለስልጣን ጀነራል ሰኢድ ስባሪ ሲናገሩ እነዚህ ሰደተኞች በባህር ላይ ይጓዙ የነበረው 49 ሆነው ሲሆን በነበረው መጥፎ አየር የተነሳ ሊሰጥሙ ችለዋል:: እንደ ጀነራሉ ገለጻ የየመን መንግስት የ13 ሰዎችን ሰውነት ያተረፈ ሲሆን 9ኙ የኢትዮጵያውያን እንዲሁም 5ቱ የሶማሊያውያን ነው ተብሏል::
እንዲህ ያለው አሰቃቂ አደጋ በየመን አካባቢ ሲደርስ በ6 ወር ጊዜያት ውስጥ ለ3ኛ ጊዜ ሲሆን ባለፈው ዲሴምበር 12 የየመን መንግስት የ24 ኢትዮጵያውያንን አስከሬን ከባህር እንዳወጣ; እንዲሁም በጁላይ 12 70 ኢትዮጵያውያን እንዲሁ በቀይ ባህር ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም::
እንደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት መግለጫ በዚሁ በቀይባህር በኩል ተሻገረው ወደ የመን ከሚሄዱ አፍሪክውያን መካከል በሺህዎች የሚቆጠሩት ሕይወታቸው በአንድ ዓመት ውስጥ ያልፋል::
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment