Friday, 30 January 2015
የአንድነትና የመኢአድ ቢሮ በፖሊስ ተከቧል
የአንድነት ለፍትሕና ዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) ቢሮ በፖሊስና በደህንነት መከበቡን አቶ አስራት አብርሃ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ቢሮው በደህንነትና በፖሊስ በመከበቡ አባላት መውጣትና መግባት እንደማይችሉ የገለጹት አቶ አስራት ‹‹ውጭ ያለነው ወደ ውስጥ እንዳንገባ ተከልክለናል፡፡ ውስጥ ያሉትም መውጣት አይችሉም፡፡›› ብለዋል፡፡ የአንድነት አመራሮችና አባላት እንዳይወጡና እንዳይገቡ የከለከሉት ደህንነትና ፖሊሶች የከበባውን ምክንያት እንደማይናገሩ አቶ አስራት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ቢሮው በፖሊስና በደህንነቶች በመከበቡ አመራሮችና አባላቱ ወደ ውስጥ መግባትም ሆነ ወደ ውጭ መውጣት እንደማይችሉ ተግልጾአል፡፡
(ኢ.ኤም.ኤፍ) በቅርቡ ምርጫ ቦርድ – የአንድነት እና መኢአድ ፓርቲን መሰረዙን ገልጿል። ምርጫ ቦርድ ይህን ያደረገበት ምክንያት ለብዙዎች ግልጽ ነው። እነዚህ ሁለት ትላልቅ ፓርቲዎች ከኢህአዴግ ጋር ከጥቂት ወራት በኋላ ለህዝባዊ ምርጫ ይቀርባሉ። ምርጫውን ከተሳተፉ ደግሞ… ፓርቲዎቹ ለኢህአዴግ ስጋት ናቸው። በዚህም ምክንያት ምርጫ ቦርዱ የተለያዩ ምክንያቶች እየሰጠ ከከረመ በኋላ ሁለቱን ፓርቲዎች ከምርጫው በፊት ከጨዋታው እንዲወጡ አድርጓል።
ይህ ከመሆኑ በፊት ግን በተለይ አንድነት ፓርቲ፤ ከፓርላማው አፈ ጉባኤ ጀምሮ እስከ ምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ድረስ የተጻጻፋቸውን ደብዳቤዎች ኢ.ኤም.ኤፍ አግኝቷቸዋል። እነዚህ ደብዳቤዎች በማንበብ ወቅታዊውን የአገራችንን የምርጫ ሂደትት መገንዘብ ይቻላል። ከምንም በላይ ደግሞ ይህ ቀን ሲያልፍ ጥፋተኞች በህግ እና በታሪክ ፊት ማንነታቸው ይጋለጣል። እርስዎም ለታሪክ ምስክር ይሆንዎት ዘንድ እነዚህን መረጃዎች መጫን ወይም ለሌሎች ማካፈል ይችላሉ።
39ኙን ገጽ የደብዳቤ ልውውጥ ለማንበብ ወይም ለማውረድ ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ።
..አንድነት እና ምርጫ ቦርድ ያደረጉት የደብዳቤ ልውውጦች
.......................http://ethioforum.org/amharic/wp-
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment