Monday, 26 January 2015
የዕንቁ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር በእስር ላይ ይገኛል
የዕንቁ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆነው አቶ ፍቃዱ ማህተመወርቅ፤ የሃገር ውስጥ ገቢ መ/ቤት ‹‹ተገቢውን ግብር ለመንግሥት ገቢ አላደረክም›› በሚል ክስ ከጥር 13 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንዲውል አድርጎታል።
. አቶ ፍቃዱ ማህተመወርቅ
የዕንቁ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር በእስር ላይ ይገኛል
አቶ ፈቃዱ ከኢትዮጵያ ሆቴል በስተጀርባ በሚገኘው የቀድሞ ጉምሩክ መ/ቤት ወይም በአሁኑ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል መከላከል ዘርፍ የፀጥታና የሕግ ማስከበር ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት ቅጽር ግቢ በሚገኘው እስር ቤት የሚገኝ ሲሆን ፖሊስ ሐሙስ ጥር 14 2007 ዓ.ም ከቀኑ በዘጠኝ ሰዓት ከሠላሳ አራዳ ጊዮርጊስ ፍ/ቤት ያቀረበው ቢሆንም የዋስትና መብቱ ሳይጠበቅ ለጥር 21 ቀን ከቀትር በኋላ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶት ወደ እስር ቤት ተመልሷል።
አቶ ፍቃዱን ያሳሰረው የሃገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰቢያ መ/ቤት ‹‹የዕንቁ መጽሔት እየታተመች በነበረችበት ጊዜ የመጽሔቷ አሳታሚና ባለቤት ለመንግሥት ገቢ ማድረግ የሚገባቸውን 600 ሺኅ ብር አስቀርተዋል›› የሚል ሲሆን ፍ/ቤት ቀርቦም ‹‹ግለሰቡን በሕግ የምጠይቅበትን ሠነድ አሰባስቤ ያልጨረስኩ በመሆኑ ለሰባት ቀናት በእስር ላይ ይቆዩልኝ…›› የሚል ጥያቄ አቅርቦ ለጊዜው በፍርድ ቤቱ በኩል ተቀባይነት አግኝቷል።
የዕንቁ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆነው አቶ ፈቃዱ ማህተመ ወርቅ ‹‹ፖሊስ የመሰረተብኝ ክስ እኔን የሚመለከት አይደለም ›› ያሉ ሲሆን፤ በሕግ የሚጠየቁበት ጉዳይ ካለም የዋስትና መብታቸውን ሊያስነፍግ እንደማይችል፣ ሕጉም በአግባቡ የሚተረጎም ከሆነ ከእስር ነጻ የመሆን ዕድል እንዳላቸው ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
- See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=4118#sthash.2CpcMnqj.dpuf
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment