Monday, 16 March 2015
ሰማያዊ ፓርቲ ቅስቀሳ እንዳያደርግ እንቅፋት እየተፈጠረበት ነው
ሰማያዊ ፓርቲ ቅስቀሳ እንዳያደርግ እንቅፋት እየተፈጠረበት ነው
• የሶዶ ፖሊስ 8 የሰማያዊ ዕጩዎችን በማሰር ቅስቀሳውን አስተጓጉሏል........
• የጅማ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ተዘርፏል
..........• ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ወደ ህዝብ እንዳይደርስ ሆን ተብሎ የተቀየሰ ስልት ነው›› አቶ ስለሽ ፈይሳ
ሰማያዊ ፓርቲ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ቅስቀሳ እንዳያደርግ በፖሊሶች ክልከላና ወከባ እየደረሰበት እንደሚገኝ የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ጉዳይ ኃላፊና ም/ሊቀመንበሩ አቶ ስለሽ ፈይሳ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ዛሬ መጋቢት 5/2007 ዓ.ም ፓርቲው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ቅስቀሳ ያደረገ ሲሆን በባህርዳርና ወላይታ ዞን ፖሊስ የተለያዩ ምክንያቶችን በመፍጠር ቅስቀሰውን ማደናቀፉን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
ዛሬ ሰማያዊ ፓርቲ በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ ቅስቀሳ በሚያደርግበት ወቅት የከተማው ፖሊስ ‹‹የምርጫ ቅስቀሳ አልተጀመረም›› ብሎ ያዋከበ ሲሆን የፓርቲው አመራሮችና አባላት ቅስቀሳ መጀመሩን ገልጸው ስራቸውን እያከናወኑ በነበሩበት ወቅት ‹‹ህገ ወጥ ሰላማዊ ሰልፍ›› አድርጋችኋል በሚል ሌላ ክስ 8 የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችንና ሌሎች አባላትን በማሰር ቅስቀሳውን እንዳደናቀፈ የወላይታ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ታደመ ፈቃዱ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ በባህርዳር ከተማ ፖሊስ ‹‹በሞንታርቮ ለመቀስቀስ ፈቃድ ስላላመጣችሁ መቀስቀስ አትችሉም፡፡›› በሚል ፓርቲው ሊያደርገው የነበረውን የምርጫ ቅስቀሳ እንዳደናቀፈ የፓርቲው የምዕራብ ጎጃም ዞን ጊዜያዊ አስተባባሪ አቶ አዲሱ ጌታነህ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ‹ለምን ትከለክሏቸዋላችሁ?› በሚል ህዝቡ ፖሊሶቹን በማፋጠጡ በድምፅ መቀስቀስ ባንችልም በህዝቡ ድጋፍ የቅስቀሳ ወረቀቶችን በማሰራጨት የተሳካ ቅስቀሳ አድርገናል›› ሲሉ አቶ አዲሱ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በዚህ ወቅት ቅስቀሳ ለማድረግ ምንም አይነት ፈቃድ እንደማያስፈልግ የገለፁት አቶ ስለሽ ፖሊስ የሚፈጥረው እንቅፋት ሆን ተብሎ ሰማያዊ ወደ ህዝብ እንዳይደርስ የተቀየሰ ስልት ነው ብለዋል፡፡ ኃላፊው አክለውም ‹‹የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን በመሰረዝ ፓርቲው ምርጫው ላይ የሚፈጥረውን ጫና ለመቀነስ ጥረዋል፡፡ ይህ አልበቃ ሲልም የቅስቀሳ መልዕክቶቻችን በተደጋጋሚ በሚዲያ እንዳይተላለፉ እያደረጉ ነው፡፡ አሁን ደግሞ ወደ ህዝብ እንዳንደርስ በህገ ወጥ መንገድ በፖሊስ ማስቆም ጀምረዋል›› ብለዋል፡፡
በሌላ ዜና የጅማ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ባልታወቁ ግለሰቦች መዘረፉን የምርጫ ጉዳይ ኃላፊው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹በ02/07/07 ሁለት ሰዓት ላይ አራት ግለሰቦች ጽ/ቤቱን በመስበርና የጽ/ቤቱን ጥበቃ አስፈራርተው በማባረር ለቅስቀሳ የተላከ 6 ሺህ ኦሮምኛ በራሪ ወረቀት እንዲሁም 3 ሺህ አማርኛ በራሪ ወረቀት፣ አንድ የፎቶ ካሜራ፣ አንድ ባነር፣ ለሸካ ዞን ሊላክ የተዘጋጀ 5 ሺህ በራሪ ወረቀት፣ 50 ፖስተር፣ አንድ የእጅ ሜጋ ፎን፣ ሁለት ባነር፣ በርካታ ጋዜጦችና መጽሔቶች ሲዘርፉ የጽ/ቤቱን ኮምፒውተርም ሰብረዋል›› ..........ሲሉ ኃላፊው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
Monday, 9 March 2015
የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክት ለአራተኛ ጊዜ በሚዲያ እንዳይተላለፍ ተከለከለ
ኢቢሲ የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ መልዕክት ‹‹አላስተላልፍም›› ብሎ መልሷል
• ‹‹ኢቢሲ ከገዥው ፓርቲ ጋር ወግኗል›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ መልዕክት ‹‹አላስተላልፍም›› ብሎ መመለሱን ዛሬ የካቲት 29/2007 ዓ.ም ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ ገልጾአል፡፡ ኢቢሲ በደብዳቤው ‹‹የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በምስሉ ግርጌ የተቀመጠው እንዲሁም በቅስቀሳ መልዕክታችሁ ውስጥ አልፎ አልፎ የሚታየው ሰንደቅ አላማ ምስል የሀገሪቱን ሰንደቅ አላማ የማይወክልና ህገ መንግስቱን…. የሚፃረር ሆኖ አግኝተነዋል›› በሚል እንደማያስተላልፍ ገልጾአል፡፡
በሌላ በኩል ‹‹ይህ የኢቢሲ ተግባር የሰማያዊን ፕሮግራም ላለማስተላለፍ ሆን ተብሎ የተሰጠ ሰበብ ነው›› ያለው የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ በህገ መንግስት የተከለከለውን ቅድመ ምርመራ ኢቢሲ እየተገበረው ነው ሲል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
‹‹ህግ ተጥሷል ከተባለ እንኳን ፕሮግራሙ ከተላለፈ በኋላ እንከሰስ ነበር እንጅ ባልረባ ምክንያት አላስተላልፍም ብለው መመለስ አልነበረባቸውም›› ያለው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ሰንደቅ አላማ የሚውለበለበውን እንጅ ከዛ ውጭ ያለን ማናቸውንም ነገር የሚመለከት አይደለም ሲል ኢቢሲ የፓርቲውን መልዕክት ላለማስተላለፍ ያቀረበውን ሰበብ ተችቷል፡፡ አቶ ዮናታን አክሎም ‹‹በአዋጅ 654/201 ላይ የሰፈረው ህግ አንድም ቦታ ተሰቅሎ ስለሚውለበለብ፣ ከመኪና ከሚውለበለብ እና በአደባባይ ከሚያዝ ሰንደቅ አላማ ውጭ ስለ ሌላ አንዳችም የሚከለክለው ነገር የለም፡፡ ስለዚህ ኢቲቪ ለገዥው ፓርቲ በመወገን ፕሮግራማችን እንዳይተላለፍ እያደረገ ነው›› ሲል ወቅሷል፡፡
በተያያዘ ዜና ፓርቲው ነገ የካቲት 30 በሬድዮ ፋና ከአንድ ሰዓት ዜና በኋላ ለሚተላለፈው ፕሮግራም ትናንት ስድስት ሰዓት መልዕክቱን ለራዲዮ ጣቢያው ለማስገባት ቢሞክርም ‹‹ዘግተው ወጥተዋል፣ ሰኞ ነው የሚገቡት፡፡ ሰኞ አስገቡ›› በሚል የሰማያዊ ፓርቲን መልዕክት መልሰዋል፡፡የፓርቲዎች መልዕክት ከሚተላለፍበት 36 ሰዓት ቀድሞ እንዲገባ እንደተባለ የገለጸው አቶ ዮናታን ሰኞ ጠዋት የሚተላለፍን መልዕክት ‹‹ሰኞ ጠዋት አምጡ›› ብሎ መመለስ ላለማስተላለፍ እንደወሰኑ ያሳያል ብሏል፡፡
ከአሁን ቀደም ኤፍ ኤም 96.3 ሁለት ጊዜ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ አገልግሎት አንድ ጊዜ የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ መልዕክት የመለሰ ሲሆን ይህኛው ለአራተኛ ጊዜ መሆኑ ነው፡፡
Monday, 2 March 2015
በአዲስ አበባ የመኪና አደጋው በፎቶ ግራፍ
ዘ-ሐበሻ በተደጋጋሚ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተከሰቱ ስላሉ የመኪና አደጋዎች እርምት እንዲወሰድ ከሚል አንፃር ስትዘግብ ቆይታለች:: በኢትዮጵያ ባፈለው ዓመት ብቻ ከ3 ሺህ በላይ ዜጎች በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው ሲያጡ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል። ከዚህ ውስጥ 3 ሺህ 331 ሰዎች በአደጋው ህይወታቸውን ሲያጡ ከ11 ሺህ በላይ ደግሞ ለከባድና ለቀላል የአካል ጉዳት መዳረጋቸው ተዘግቧል፡፡ የኢትዮጵያ ትራፊክ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ ደግሞ በኢኮኖሚው ላይ እያሳደረ ያለው ጉዳት ከባድ ነው ይላል;; ዝርዝሩን ያንብቡ
ዘ-ሐበሻ) በኢትዮጵያ በየቀኑ እየደረሱ ያሉ የመኪና አደጋዎች ቁጥር ከ እለት ወደ እለት እየጨመረ መሄዱ ነዋሪዎችን በከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደከተተ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ይናገራሉ:: በዚህ በዘ-ሐበሻ ድረገጽ ላይ እንኳ በጊዜው ስለመኪና አደጋዎችና ስለሚወድመው የሰው ሕይወትና ንብረት በተደጋጋሚ ጽፈናል:: አሁን ደግሞ ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው አራት ኪሎ የድል ሐውልት አደባባይ አካባቢ ከስድስት ኪሎ መስመር ወደ ለገሀር ይጓዝ የነበረ የአንበሳ ከተማ አውቶቡስ ባገጠመው የፍሬን ችግር ከአንድ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ የሁለቱም ተሽከርካሪ ሹፌሮች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል::
በዚህ የመኪና አደጋ በተሳፋሪዎች ላይ የደረሰ ጉዳት ባይኖርም አደጋው በፎቶ ግራፍ ላይ እንደምትመለከትት በጣም አሰቃቂ ነበር:: ከስድስት ኪሎ ከሚገኘው ቤታቸው ሃገር አማን ብለው ወደ ሥራቸው በማሽከርከር ላይ የነበሩትና ጉዳት የደረሰባቸው አቶ ግርም ጎርፉ የተባሉ ግለሰብ የአንበሳ አውቶቡሱ ድንገት መስመሩን ስቶ በመምጣት እንደገጫቸው ገልጸዋል::
....በአዲስ አበባ አንበሳ አውቶቡሱ መንገድ ስቶ የቤት መኪናውን ገጨ...
ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ከተማ ከካራ ቆሬ ወደ ለገሃር ሲጓዝ የነበረ አውቶቡስ ዘነበወርቅ አለርት ሆስፒታል ፊትለፊት ረዥም ድልድይ ውስጥ ገባ፤ በዚህ አሰቃቂ አደጋ ስምንት ሰዎች መሞታቸው ይፋ ሆነ። አውቶቡሱ ቁጥራቸው እስካሁን በውል ያልታወቁ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ይጓዝ የነበረ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ሲያስታውቅ የአውቶቡሱ ቁጥር 66 እንደሆነ ታውቋል። ካራ ቆሬ ወደ ለገሃር ሲጓዝ ዘነበወርቅ አለርት ሆስፒታል ፊት ለፊት ባለው ረዥም ድልድይ ውስጥ በገባው አውቶቡስ የተነሳ በአደጋው እስካሁን አንድ እግረኛን ጨምሮ አራት ወንድ እና አራት ሴት ተሳፋሪዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ሲገለጽ 46 የሚሆኑት ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ዘ-ሐበሻ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል። የአውቶቡሱ ሹፌር እና ትኬት ቆራጭ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በሕይወት ተርፈዋል። የአውቶቡሱ አደጋው መንስኤ ላይ መሆኑ ሲታወቅ በአውቶቡሱ ድልድይ ውስጥ መግባት ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑ ዘ-ሐበሻ ጨምሮ የደረሳት ዜና ያስረዳል።
....ዘነበወርቅ ድልድልይ የገባው አውቶቡስ ሲወጣ
Tuesday, 24 February 2015
የኬንያ ፖሊስ 101 ኢትዮጵያዉያንን አሠሩ
ናይሮቢ፤ የኬንያ ፖሊስ 101 ኢትዮጵያዉያንን ማሠሩ
የኬንያ ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ ወደደቡብ አፍሪቃ ሊጓዙ ነበር ያላቸዉን ከመቶ የሚበልጡ ኢትዮጵያዉያንን ትናንት ማምሻዉን ማሠሩን አሶሲየትድ ፕረስ ከናይሮቢ ዘገበ። የኬንያ ልዩ የወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ኖህ ካቱሞ ለዜና ወኪሉ ዛሬ እንደገለፁት የታሠሩት 101 ወንዶች ኢትዮጵያዉያንና እነሱን በኬንያ ድንበር በኩል ሊያሾልኩ በመሞከር የተጠረጠሩ ሶስት ኬንያዉያን ናቸዉ። ካቶሙ እንዳሉት ኢትዮጵያዉያኑ ወደደቡብ አፍሪቃ ጉዟቸዉን ከመቀጠላቸዉ በፊት በቡድን በቡድን ሆነዉ ኬንያ መዲና ናይሮቢ በሚገኝ አንድ ቤት ዉስጥ አርፈዉ ነበር። ታሳሪዎቹ ዳኛ ፊት ቢቀርቡም እንግሊዝኛ ስለማይረዱና በአማርኛም የሚያስተረጉምላቸዉ ባለመገኘቱ ምክንያት ለጊዜ ክስ አልተመሠረተባቸዉም። እንደዘገባዉ ዳኛዉ ቪክቶር ዋኩሜሌ አስተርጓሚ እስኪገኝ ጉዳዩን ለነገ ቀጥረዋል። ከዚህ ቀደምም ለተመሳሳይ ጉዞ የተዘጋጁ 95 ኢትዮጵዉያን በኬንያና ታንዛንያ ድንበር አቅራቢያ መታሠራቸዉ ተዘግቧል። የኬንያ ፖሊስ ከአፍሪቃ ቀንዷ ሀገር ሰዎችን የሚያሸጋግሩት ወገኖች ኢትዮጵያዉያኑን በሕገ ወጥ መንገድ የሚያዘዋዉሩት የጦር መሣሪያ፣ አደንዛዥ እፆች፣ የዝሆን ጥርስና የመሳሰሉትን ነገሮች አስርገዉ በሚያስገቡበትና በሚያወጡበት መስመር እንደሆነ ገልጿል። ...... source.-www.dw.amharic
ከሜድትራኒያን ሞት ፊት የቆሙት ስደተኞች
ባለፈው የጎርጎሮሳውያኑ አመት የሜድትራኒያን ባህርን በጀልባ ለማቋረጥ ከሞከሩ 218,000 ሰዎች መካከል 3,500 መሞታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን አስታውቋል። በዚህ በተመሳሳይ መንገድ ወደ አውሮጳ ለመሻገር የሚሞክሩ ስደተኞች ቁጥር በአሳሳቢ ደረጃ በመጨመር ላይ ነው።
ሰለሞን መንግስቴ በሊቢያዋ የቤንጋዚ ከተማ ባለቤቶቹ ጥለውት የሄዱትን ቤት ይንከባከባል።አትክልት ይኮተኩታል። ግቢውን ያጸዳል። ሰለሞን በቤንጋዚ ብቻውን አይደለም። ባለቤቱ የዝና እዘዘው ቀን ቀን ከሰው ቤት ትሰራለች። ሰለሞን ስለ ወርሃዊ ደሞዙ ሲጠየቅ ፈገግ እያለ «በእውነት መቼ እንደሚከፍሉኝም አላወኩም።» ሲል ይመልሳል።
ሰለሞን ተወልዶ ካደገበት የጎንደር አካባቢ ወደ ሱዳን ገዳሪፍ የተጓዘው ለደላሎች አምስት ሺ የኢትዮጵያ ብር ከፍሎ በአስቸጋሪ የሌሊት ጉዞ ነበር። ጉዞውን ያመቻቹለት የኢትዮጵያ እና የሱዳን ህገ-ወጥ ደላሎች ነበሩ። «ጉዞው የሚጀመረው ለሊት ሰው በሌለበት ሰዓት በእግር ነው። የሚለው ሰለሞን መንገዱ ከሶስት እስከ ሰባት ቀናት ሊወስድ እንደሚችል ይናገራል። ከገዳሪፍ በኋላ በመኪና የሚደረገው ጉዞ «ሰው በሰው ላይ ጭነው ስለተጓዝን በእግር ከተደረገው የበለጠ ያስከፋል።»ሲል ያስታውሳል።
በተመሳሳይ መንገድ ከኢትዮጵያ ከወጣችው ከባለቤቱ የዝና እዘዘው ጋር የተዋወቁት በሱዳን በቤተ-ክርስቲያን ነበር። ሁለቱ ስደተኛ ወጣቶች መስከረም 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ሶስት ጉልቻ መሰረቱ። ከ2003-2006 ዓ.ም. የዝና በሰው ቤት ሰለሞን ተመላላሽ ስራ እየሰሩ ቢቆዩም ሃገሩ አልተመቻቸውም። እንደገና ሌላ መንገድ-ሌላ ጉዞ አሁንም በህገ-ወጥ መንገድ
ከሱዳን ወደ ሊቢያ ለመጓዝ ለህገ-ወጥ ደላሎች በነፍስ ወከፍ ስድስት ሺ በአጠቃላይ አስራ ሁለት ሺ የሱዳን ፓውንድ ከፍለዋል። ሰለሞን ከባለቤቱ ጋር ከሱዳን ተነስተው የሰሐራ በርሃን ሲቋርጡ ጉዞውን ያመቻቹትን ሰዎች «አይን ያወጡ ደላሎች » ሲል ይገልጻቸዋል። 9.4 ሚሊዮን ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሰፋውን የሐራ በርሃ ማቋረጥ ለጥንዶቹ መራር ነበር። «አንዲት ዛፍ ለውርርድ የማታይበት» ይለዋል ሰለሞን የሰሐራ በርሃን። የዝና እዘዘው ከሱዳን ወደ ሊቢያ ላደረጉት ጉዞ ዋንኛ ምክንያታቸው «ዞሬ ወደ አገሬ ብመለስ ምን ይዤ ልመለስ? » የሚለው ጥያቄ ትልቅ ቦታ እንደነበረው ታስታውሳለች። ስምንት ቀናት የፈጀውን ጉዞ ስታስታውስ ሲቃ ይተናነቃታል። ከበርሐው ንዳድ እና ውሃ ጥም ባሻገር ከውስጧ ሃዘን የቀበረ ትዝታ አላት። « ስንት እህቶቻችንን በበርሐ ጥለናቸው መጥተናል። እህቴ ወንድሜ አትልም። እህቴ ተኝታ ብትቀር አትቀሰቅስም።» ስትል ስለተሻገረችው የበርሐ ሞት ትናገራለች። ከሱዳን ወደ ሊቢያ በነበረው ጉዞ ስደተኞችን ከጫኑ ሶስት መኪኖች መካከል አንዱ ተገልብጦ ብዙዎች ማለቃቸውን ሰለሞን ያስታውሳል።
ሰለሞን እና እዝና የሰሐራ በርሃን አቋርጠው ሊቢያ ሲገቡ ከለበሱት ልብስ በቀር በእጃቸው አንዳች ነገር አልነበረም። ውስን ምግብ፤አልባሳት እና የግል ንበረቶች የያዙባቸው ሻንጣዎች መንገድ መቅረታቸውን እዝና ተናግራለች። እናም ሁለቱ ወጣት ጥንዶች ሊቢያ ሲደርሱ ፓስፖርትም ይሁን የጉዞ ሰነድ በእጃቸው አልነበረም።
የሊቢያ ሁለተኛ ከተማ የሆነችው ቤንጋዚ እንደ ቀድሞ ሰላም እና መረጋጋት ርቋታል። ነዋሪዎቿ የመኖሪያ ቤታቸውን ጥለው ተሰደዋል።ሰለሞን እና የዝና በቤንጋዚ የበረከተው የጥይት ተኩስ እና ሞት ስጋት ፈጥሮባቸዋል። እናም ሜድትራኒያን ባህርን ተሻግረው አውሮጳ ሊገቡ ቆርጠዋል።ሰለሞን «አሁን ካለንበት ቢንጋዚ የእቃ መርከብ ይመጣል ይባላል። ግን አይገኝም። እሱ 1,500 ዶላር ነው። ከደላላው ጋር ተነጋግረናል። በመጣ ጊዜ እነግራችኋለሁ ብሎናል።» ሲል የመጀመሪያ አማራጫቸውን ያስረዳል። ሁለተኛ አማራጫቸው አሁን ካሉበት ቤንጋዚ ከሊቢያዋ ዋና ከተማ 50 ኪ.ሜ. ወደ ምትርቀው ጋሪቡሊ መጓዝ ይኖርባቸዋል።«ከጋሪቡሊ ትልቅ የሚባለው እስከ 1,500 ዶላር የሚከፈልበት ነው። መካከለኛ የሚባለው ከ900-1100 ዶላር የሚከፈልበት ሲሆን አነስተኛ የሚባለው እና ብዙ ጊዜ አደጋ ደረሰባት የሚባለው ጀልባ ጉዞ ሰባት መቶ እና ስምንት መቶ ዶላር ያስከፍላሉ።» የሚለው ሰለሞን ጉዞው አስራ ስምንት ሰዓታት እንደሚወስድም መረዳታቸውን ተናግሯል።
ሰለሞንም ሆነ እዝና በጉዞው ስለሚገጥማቸው መከራ ጠንቅቀው ያውቃሉ። እዝና ከለቅሶዋ ጋር እየታገለች ሌላ ምንም አማራጭ እንደሌላቸው ታስረዳለች። «ምን ይዤ?» ከሚለው የኢኮኖሚ ጥያቄ ባሻገር በእጃቸው የጉዞ ሰነድ ባለመኖሩ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ቢያስቡ እንኳ ያለፉበትን መራራ ጉዞ መድገም ይኖርባቸዋል።ሰለሞን «አቅጣጫ የመሳት፤የመናወጥ፤ብርድ፤የመገልበጥ እና የመዋጥ ችግር እንዳለ እንሰማለን። እንዲህ አይነት እጣም የሚደርሳቸው ሰዎች እንዳሉ እንያወቅን ነው። ከሞት ጋር እየተነጋገርን ነው ማለት ትችላለህ።» ሲል ተናግሯል።
በዚህ ወር ብቻ ከሊቢያ ወደብ ተነስተው የሜድትራኒያን ባህርን በማቋረጥ ወደ ጣሊያን ለመሻገር የሞከሩ 300 ስደተኞች ለሞት ሳይደረጉ እንዳልቀረ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን አስታውቋል። ባለፈው አመት ብቻ 218,000 ሰዎች የሜድትራኒያን ባህርን በጀልባ አቋርጠዋል። 3,500 ያህሉ ግን ከጉዞው መጨረሻ መድረስ ሳይችሉ በባህሩ ላይ ህይወታቸውን አጥተዋል። ሰለሞን እና የዝና በጉዞው ሊገጥማቸው የሚችለውን ሁሉ ጠንቅቀው ያውቃሉ። ቢሆንም ፓስፖርትም ይሁን ህጋዊ የጉዞ ሰነድ በእጃቸው ባይኖርም ጉዞ ለመጀመር ዝግጅት ላይ ናቸው።
እሸቴ በቀለ
ሒሩት መለሰ
Saturday, 21 February 2015
ሰበር ዜና – የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በዕጩነት እንዳይቀርቡ ተደረገ
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በዕጩነት እንዳይቀርቡ ተደረገ
‹‹ምርጫ በህዝብ ፍላጎት ሳይሆን በሎተሪ ሆኗል›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት አዲስ አበባ ከተማ ወረዳ 5 ለመጭው ምርጫ ለተወካዮች ምክር ቤት ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው ሊቀርቡ የነበሩት የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹ከቀረቡት 17 ዕጩዎች መካከል በተጣለ ዕጣ ወድቀዋል›› በመባላቸው ለመጭው ምርጫ በዕጩነት እንዳይቀርቡ መደረጋቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል በዕጩነት በቀረቡበት ወረዳ 5 የምርጫ ጣቢያ ኢህአዴግ፣ የትግስቱ አንድነት፣ ቅንጅትን ጨምሮ ሌሎች ስድስት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ያለ ምንም ዕጣ አልፈዋል የተባለ ሲሆን ‹‹የሚያልፉት በዕጣ ነው›› የተባሉት ሰማያዊን ጨምሮ 11 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች መካከል ሰማያዊና ሌሎች አራት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ‹‹ዕጣ አልወጣላቸውም፡፡›› ተብሏል፡፡ ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹ሰማያዊ ህዝብ ውስጥ በሰፊው እየገባና እያንቀሳቀሰ ያለ ግንባር ቀደም ፓርቲ ነው፡፡ እንደ ኢህአዴግ ያሉን ጨምሮ ዕጣ ውስጥ አይገቡም፡፡ ሰማያዊ ደግሞ ይህ ነው የሚባል እንቅስቃሴ ከማያደርጉት ፓርቲዎች ጋር ዕጣ ውስጥ ገብቶ ወደቀ መባሉ ዴሞክራሲ ከጅምሩ ጀምሮ የህዝብ ድምጽ ሆኖ እያለ በእኛ አገር ሎተሪ ሆኗል ማለት ነው፡፡›› ብለዋል:: ሊቀመንበሩ አክለውም ‹‹ሂደቱ ምንም ይሁን ምን አንድን ፓርቲ ወይንም ተወካይን ህዝብ ነው መምረጥ ያለበት፡፡ ህዝብ የሚፈልገውና የሚመረጥ ፓርቲ ነው ለምርጫ መቅረብ ያለበት፡፡ አሁን ግን እየተባለ ያለው በአንድ በኩል ህዝብ የማይፈልገው ያለ ዕጣ ሲገባ፣ በሌላ በኩል ህዝብ የሚፈልገው ሰማያዊን የመሰለ ፓርቲ ዕጣ ውስጥ ገብቶ አላለፈም እየተባለ ነው፡፡ በአንድ በኩል ህዝብ የተማረረባቸው ያለ ቅድመ ሁኔታ ህዝብን እንደሚያንቀሳቅስ የሚታወቀው ሰማያዊ ደግሞ ህዝብ ስፈለገው አሊያም በጥንካሬው ሳይሆን በሎተሪ ወድቀሃል ተብሏል›› ሂደቱ የተሳሳተ ነው ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/

Thursday, 12 February 2015
አቶ ጸጋዬ አላምረው የእሥር ማዘዣ በመዉጣቱ አገር ለቀው ተሰደዱ
የእሥር ማዘዣ በመዉጣቱ አቶ ጸጋዬ አላምረው አገር ለቀው ተሰደዱ
የአንድነት ፓርቲ ምክትል አፈጉባኤ የሆኑትና በቅርቡ ሰማያዊ ፓርቲ የተቀላቀሉት አቶ ጸጋዬ አላምረው፣ ከወያኔ የፀረ-ሽብር ግብረ ኅይል እንዲታሰሩ የማዘዣ ወረቀት በመዉጣቱ፣ ለተወሰነ ቀናት አገር ቤት ራሳቸውን ሰዉረውከቆዩ በኋላ፣ በአሁኑ ጊዜ ከኢትዮጵያ ዉጭ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።
አቶ ጸጋዬ የአንድነት ፓርቲ የፋይናንስ ሃላፊ ሆነው የሰሩ ሲሆን፣ አቶ ሃብታሙ አያሌው ከታሰሩ በኋላ የመኢአድ አመቻች ኮሚቴ ዋሃ ሰብሳቢ ሆነው ሰርተዋል።፣ ሕወሃቶች መሰናክል ፈጠርበት እንጂ በመኢአድ እና በአንድነት መካከል ዉህደቱ ጫፍፍ እንዲደርስ፣ ቁልፍ ሚና ከተጫወቱ የአመራር አባላት መካከል አንዱ ነበሩ። የአንድነት ፓርቲ ያደርግ በነበረው የምርጫ ዘመቻም፣ የምርጫ ኮሚቴ አባል በመሆን ትልቅድርጅታዊ ሥራ ይሰሩም ነበር።
የአንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ ጠርቶት በነበረው ሰልፍ ፣ የሕወሃት ታጥቂዎች በሰላማዊ ዜጎችን ላይ ኢሰባአዊ የሆነ ከፍተኛ ድብደባ በፈጸሙበት ወቅት፣ በአካል ከተጎዱት ወገኖች መካከል አንዱ አቶ ጸጋዬ ነበሩ። ከስድስት ወራት በፊትም በግንቦት ወር 2006 ዓ.ም፣ አንድነት እና መኢአድ የቅድመ ዉህደት ፊርማ በፈረሙበት ጊዜም፣ የአገዛዙ ካድሬዎች ስብሰባዉ ለመረበሽ በሞከሩበት ወቅት ተፈንክተው ትልቅ ጉዳት ደሮባቸውም ነበር።
ሕወሃቶች በአቶ ጸጋዬ ላይ ያነጣጠሩት፣ በርካታ የአንድነት አባላትን ይዘው አቶ ፀጋዬ ሰማያዊን ከተቀላቀሉ በኋላ ሲሆን፣ ዋና ክስ አድርገው የወሰዱትም “አንድነት ፓርቲ የገንዘብ እርዳታ ከሽብርተኞች ይቀበላል፣ የሚቀበለዉም በአቶ ጸጋዬ አላምረው በኩል ነበር” የሚል እንደሆነ ታውቋል። ሕወሃቶች በሚቆጣጠሩት ኢቲቪና ራዲዮ ፋና ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ በአንድነት ላአይ የጅመሩ ሲሆን፣ እነ ትግስቱ አወሉንም በሜዲያ፣ የአቶ ጸጋዬ አላምረዉን ስም እየጠሩ “ገንዘብ ተቀባይ እርሱ ነበር” እያሉም እንዲናገሩ እያደረጓቸው ነው።
የአንድነት ፓርቲ በዉጭ አገር ካሉ ኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ ያገኝ እንደነበረ ይታወቃል። በዉጭ ያሉ የአንድነት ድጋፍ ድርጅቶችም፣ ከቅንጅት ጊዜ ጀምሮ በሰማዊ ትግል የሚያምኑ እንደመሆናቸው፣ በነርሱ በኩል ተሰብስቦ የሚላክን ገንዘብ ከሽብርተኞች እንደመጣ አድርጎ መቁጠር በሕግ፣ በሞራልም በአሰራር ተቀበያነት እንደሌላው የድጋፍ ድርጅቱ አባላት ይናገራሉ።
- source,-www.zehabesha.com
Wednesday, 11 February 2015
በዩኒቨርሲቲው ጥበቃ የአንዱ ተማሪ ሕይወት አለፈ
በዩኒቨርሲቲው ጥበቃ ከተደበደቡት ተማሪዎች መካከል የአንዱ ሕይወት አለፈ
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ ናቸው
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት አካባቢ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ፋኩልቲ፣ ሁለት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው የጥበቃ ሠራተኛ ድብደባ ተፈጽሞባቸው አንደኛው ሕይወቱ ማለፉ ተረጋገጠ፡፡
ጥር 23 ቀን 2007 ዓ.ም. የግማሽ ዓመት ፈተናቸውን ካጠናቀቁት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መካከል፣ ሙሉቀን ከበደና ታምራት አባተ የተባሉ ተማሪዎች በዕለቱ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ታውቋል፡፡ ተማሪዎቹ ፈተናቸውን እንዳጠናቀቁ ከግቢ ወጥተው ሲዝናኑ ካመሹ በኋላ ወደ ማደሪያ ክፍላቸው ሲመለሱ፣ ፀደቀ አድማሱ ከሚባለው ተጠርጣሪ የጥበቃ ሠራተኛ ጋር መጋጨታቸውን ከፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ተማሪዎቹ ወደ ዩኒቨርሲቲው ግቢ ሊገቡ ሲሉ ተጠርጣሪው እንዲቆሙ ሲያደርጋቸው ተማሪ መሆናቸውን የሚያረጋግጡበትን መታወቂያ ቢያሳዩም፣ ከተጠርጣሪው ጋር ሊግባቡ ባለመቻላቸው ድብድቡ መጀመሩ ታውቋል፡፡ ተጠርጣሪው በወቅቱ ይዞት በነበረው የእንጨት ዱላ ደጋግሞ ሲደበድባቸው የተመለከተ ሾፌር፣ ሌሎች የተኙ ጥበቃዎችን በማስነሳቱ የተፈጠረው ድብድብ የቆመ ቢሆንም፣ ተማሪዎቹ በደረሰባቸው ድብደባ ተጎድተው ስለነበር በአቅራቢያቸው በሚገኘው ጥሩነሽ ቤጂንግ ጠቅላላ ሆስፒታል መወሰዳቸውም ተጠቁሟል፡፡
ታምራት አባተ የተባለው ተማሪ በጥሩነሽ ቤጂንግ ጠቅላላ ሆስፒታል በተደረገለት ሕክምና የተረፈ ቢሆንም፣ የደረሰበት ድብደባ ከባድ በመሆኑ ለተጨማሪ ሕክምና ሪፈር የተደረገው ተማሪ ሙሉቀን፣ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሕክምና ላይ እያለ ጥር 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ሕይወቱ ማለፉ ታውቋል፡፡ ፖሊስ በድብደባው ተሳትፈዋል በማለት በቁጥጥር ሥር ያዋላቸውን ተጠርጣሪ የዩኒቨርሲቲውን የጥበቃ ሠራተኞችን ፍርድ ቤት አቅርቦ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ በመጠየቅ በምርምራ ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡
- See more at: http://satenaw.com/amharic/
Tuesday, 10 February 2015
አባዱላ ገመዳ የሃሰት ዲግሪዎችን ሸምተው መጠቀማቸው ተረጋገጠ
አበበ ገላው በአባዱላ ገመዳ 2 የውሸት ዲግሪዎች ግዢ ዙሪያ ማስረጃዎችን ለቀቀ
(አዲስ ቮይስ) የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ የሆኑት አባዱላ ገመዳ በኢንተርኔት ያለምንም ትምህርት ዲግሪ በመሸጥ ከሚታወቅ አንድ የዲፕሎማ ወፍጮ ቤት (diploma mill) የሃሰት ዲግሪዎችን ገዝተው መጠቀማቸውን አዲስ ቮይስ አረጋገጠ።
አፈጉባኤው የባችለርስ ዲግሪ እ.ኤ.ኤ በ2001 እንዲሁም የማስተርስ ዲግሪ በ2004 አሜሪካን አገር በሚኖረውና አሊ ሚርዛኢ በሚባል ኢራናዊ ከሚንቀሳቀሰው “አሜሪካን ሴንቸሪ ዩኒቨርሲቲ” (ሴንቸሪ ዩኒቨርሲቲ) ያለምንም ትምህርት መግዛታቸው በመረጃ ተረጋግጧል። አባዱላ ሁለቱንም ዲግሪዎች የህዝብ አስተዳደር ትምህርት ተምረው አንዳገኟቸው ሲገልጹ የቆዩ ሲሆን ይህንንም በፓርላማ ድረገጽ፣በፌስቡክ፣ ዊኪፔድያ፣ በመንግስትና በግል የመገናኛ ተቋማት በይፋ ታትሞ እንዲሰራጭ አድርገዋል። ከዚህም በተጨማሪ ከቻይና መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የባችለርስ ዲግሪ እንዳገኙ በህይወት ታሪካቸው ላይ በይፋ ያሰፈሩ አባዱላ እንዲህ አይነት ዲግሪም ይሁን ትምህርት ከቻይና የትምህርት ተቋም አለማግኘታቸው ታውቋል።
ሴንቸሪ ዩኒቨርሲቲ ከማንም እውቅና ያልተሰጠው ሲሆን አሊ ሚርዛኢ በዋነኛነት ከቤቱ የዲግሪ ሽያጭ እንደሚያከናውን አዲስ ቮይስ በምርመራው ከማረጋገጡም በላይ ምርመራውን ደንበኛ መስሎ ላካሄደው ጋዜጠኛ አበበ ገላው የማስተርስና የዶክትሬት ዲግሪዎችን በ4000 ዶላር ሊሸጥለት ሞክሯል። ይህንንም ህገወጥ የዲግሪ ሽያጭ የሚያረጋግጡ በርካታ የኢሜይልና የሰነድ መረጃዎች ጋዜጠኛው እጅ ገብተዋል።
ከሁለት ሳምንታት በፊት የህወሃቶች ቁንጮ ምሁራን ተደርገው ይቆጠሩ ከነበሩት አንዱ ቆንስጣንጢኖስ በርሄ የማስተርስና የዶክትሬት ዲግሪ ከሴንቸሪ ዩኒቨርሲቲ ገዝተው እራሳቸው በዶክተርነትና በፕሮፌሰርነት መሾማቸው መጋለጡ ይታወሳል። በኢትዮጵያ ወንጀለኛ መቅጫ ህግ የሃሰት ዲግሪና ሰርተፍኬት ተጠቅሞ ለራስም ሆነ ለሌሎች ጥቅም ማግኘትና ማስገኘት በማጭበርበር ወንጀል የሚያስከስ ስና እስከ አንድ አመት እስር የሚያሰቀጣ ድርጊት ነው።
የሴንቸሪ ዩኒቨርሲቲ ባለቤት ከዚህ በፊት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈጽም ተደርሶበት በባለቤትነት ሲመራው የነበረው የሃዋይ ቢዝነስ ኮሌጅን እኤአ 2007 እንዲዘጋ ተደርጓል።
በኢፌዲሪ ህገ መንግስት መሰረት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛው የስልጣን አካል ሲሆን አፈጉባኤው ዋነኛው ህግ አውጭ ተደርጎ ይቆጠራል። የዛሬ አራት አመት አፈጉባኤ ሆነው የተሾሙት አባዱላ ገመዳ ትምርታቸው ከ፰ኛ ክፍል አቋርጠው የደርግ ወታደር ሆነው የነበር ሲሆን በኤርትራ በሻቢያ ተማርከው የነበረ ሲሆን በህወሃትና በሻቢያ መካከል በተደረገ ስምምነት መሰረት ከ እነ አቶ ኩማ ደመቅሳ ጋር ለህወሃቶች ተላልፈው ከተሰጡ በሁዋላ የ ኦህዴድ መሪና መስራች እንዲሆኑ ተደርጓል።
የእነ አባዱላን ዲርጊት አሳፋሪ ሲሉ የገለጹት እውቁ ጋናዊው ምሁር ፕሮፌሰር ጆርጅ አይቴ እንዲህ አይነት እርካሽ የማጭበርበርና የማስመሰል ድርጊት የስር አቱን ንቅዘት ፍንትው አድርጎ አንደሚያሳይ ገልጸዋል። ፕሮፈሰሩ ተጠያቂነት የሌለው ህገውጥነት የ አንባገነኖች ባህሪ መሆኑን አስገንዝበው እንዲ አይነትኞቹ አጭበርባሪ የስልጣን ጥመኞች ለውጥ ፈላጊ በሆነው አዲስ ትውልድ መተካት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
አይቴ አገር ለመምራት የምያስፈልገው እውቀት እንጂ ዲግሪ አይደለም ብለዋል። “ዲግሪ መግዛት ይቻላል፣ እውቀት ግን ፈጽሞ አይገዛም” በማለት የእነ አባዱላን ድካም ከንቱነት ጠቁመዋል።
የቀድሞው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ሚኒስቴር ዴታ የነበረው ኤርምያስ ለገሰ በበኩሉ አባዱላ በራስ መተማመን የሌለው የሃሰት ስብእና በህወሃቾች የተፈጠረለት ግለሰብ በመሆኑ ያንን በዲግሪ ጋጋታ ለመሸፈን የሚያደርገው ጥረት አካል ሊሆን እንደሚችል ግምቱን ሰንዝሯል።
በርካታ ዜጎች ያለምንም ወንጀልና ጥፋት ለበርካታ አመታት ያለፍርድ በእስር በሚሰቃዩባት ኢትዮጵያ እነ አባዱላ በሃሰት ዲግሪ
አገር ሲመሩ ማየት ህዝቡን የበለጠ ለለውጥ ሊያነሳስው ይገባል ሲል አስተያተቱ ሰጥቷል።
source.- http://www.zehabesha.com/amharic/archives/38893
Monday, 9 February 2015
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጥሰት ዙሪያ መከረ
ኢሳት ዜና
ህብረቱ ጥር 27፣2007 ዓም በብራሰልስ ቤልጂየም የአውሮፓ ህብረት ጽ/ቤት ውስጥ ለ3 ሰአታት ባደረገው የኢትዮጵያ የሰአብአዊ መብት ግምገማ በኦጋዴን ክልል እና በተቀሩት የኢትዮጵያ ግዛቶች በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ሰቆቃ የአውሮፓ ህብረትና አባል መንግስታት በዝምታ መመልከታቸውን ማብቃት አለበት የሚል ውሳኔ አስተላልፈዋል።
ስብሰባውን ያዘጋጁት የህብረቱ የሶሻሊስትና የዲሞክራቲክ ፓርቲዎች ጥምር ህብረት ፣ ውክልና አልባ ህዝቦች ተቆርቋሪ ድርጅት ጋር በመተባበር ነው። በስብሰባው ላይ የኦጋዴን ክልል ፕሬዚዳንት አማካሪ የነበረና በክልሉ የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በመረጃ በማጋለጥ ላይ የሚገኘው ወጣት አብዱላሂ ሃሰን፣ ተቀማጭነቱ በጄኔቫ የሆነ የአፍሪካ መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ባልደረባ፣ አቶ አብዱላሂ ሙሃመድ፣ የኦጋዴን ሴቶች ተወካይ ፣ ጋዜጠኛና የክሬት ትረስ ዳይሬክተር ግርሃም ፌብልስ፣ እንዲሁም በኦሮሞ ሴቶች ላይ የሚደረሰውን ሰቆቃ በማስመልከት ጥናት ያካሄዱት፣ ዶ/ር ባሮ ቀኖ በቪዲዮ የተደገፈ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተዋል።
እንግሊዛዊው ግራሃም ፌብልስ በኢትዮጵያ 2 አመታት ቆይታቸው የታዘቡትን የሰብአዊ መብት ጥሰቶች በተለይም በኦጋዴን ክልል በሴቶች ላይ ተፈጽሟል ያሉትን አስገድዶ መድፈር ወንጀል የታዳሚውን ስሜት በነካ መልኩ አቅርበዋል። በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በዜጎች ላይ ሽብርን እያካሄደ ነው ያሉት ሚ/ር ፌብልስ የዚህ ሰቆቃ ፈጻሚዎች፣ ከአውሮፓ ህበረትና መንግስታት በያመቱ ከፍተኛ የገንዘብ እርዳታ የሚያገኙ መሆናቸው እጅግ የሚያሳዝነው ነው ብለዋል።
በጉባኤው ላይ የኦጋዴን ነጻነት ግንባር ተወካይ ዶ/ር ባዳል አህመድ እና አርበኞች ግንቦት7 ተወካይ አቶ አበበ ቦጋለ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸመ ነው የሚሉትን የሰብአዊና የፖለቲካ መብቶች እረገጣና አስከፊ ሰቆቃ በእየተራ አቅርበዋል።
የአውሮፓ ህብረትን ወክለው በስብሰባው ላይ የተገኙት ወ/ሮ አና ጎሜዝና የእንግሊዝ የፓርላማ ተወካይ ወ/ሮ ጁሊ ዋርድ በየተራ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ መንግስት ከ60 በመቶ በላይ በጀቱን ከአውሮፓ ህበረት እየተቀበለ ዜጎች ላይ እየፈጸማቸው ያለው አስከፊ ሰቆቃዎችን አውሮፓ ካሁን በሁዋላ በዝምታ ማየት የለባትም ካሉ በሁዋላ፣ ኢትዮጵያኖች በአገራቸው እየተፈጸመ ያለውን አፈናና ጭቆና የውጭ ማህበረሰብ ያስቆምልናል ብለው ከመጠባበቅ ለራሳቸው ነጻነት ልዩነቶቻቸውን በማቻቻልና መለስተኛ ፕሮግራም በማዘጋጀት ህብረት ፈጥረው በአንድነት መታገልና ለለውጥ መነሳት አለባቸው ብለዋል።
የአውሮፓ ህብረት በዘንድሮው ምርጫ ላይ ታዛቢዎችን እንዳይልክ የወሰነው የኢህአዴግ መንግስት በየ 5 አመቱ የሚያደርገውን የተሳሳተ ምርጫ በማጀብ ህጋዊነት ለማሰጠት እንደከዚህ በፊቱ ለመተባበር ፈቃደኛ አለመሆኑን ለመግለጽ ሆኖ ሳለ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ግን ህበረቱ በገጠመው የበጀት ችግር ምክንያት ታዛቢ አልክም ብሎአል ብሎ የጀመረው ቅስቀሳ መሰረተ ቢስና የተለመደ ህዝብን የማዘናጊያ ወሬ እንደሆነ ገልጸዋል። የአመቱን 60 በመቶ የሚሸፍን በጀት የሚሰጠው ህብረቱ፣ ኢትዮጵያን የመሰለ ስትራቴጂክ አገር፣ ህብረቱ የገንዘብ እጥረት ገጥሞታል ብሎ ማሰብ ራስን እንደማታለል ይቆጠራል ብለዋል።
ህብረቱ ምርጫው ከመደረጉ ከሚቀጥለው ወር በፊት የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎችንና ሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን በስፋት የሚያሳትፍ ትልቅ ጉባኤ በሚያዚያ ወር ላይ ለመጥራት በዝግጅት ላይ እንዳለ በዚህ ስብሰባ ላይ ተገልጿል።
አንዳንድ የፓርላማ አባላት በዚህ ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ ግብጽ ህዝብ ሆ ብሎ በመነሳት ከመጪው ግንቦት ምርጫ በፊት አምባገነንነትን ከራሱ ትከሻ ላይ ለማውረድ መነሳት አለበት ሲሉ ተናግረዋል ። የኢትዮጵያ መንግስት በሚቀርብበት የሰብአዊ መብት ጥሰት ላይ አቋሙን እንዲገልጽ ቢጋበዝም ፣ ፈረንሳይኛ ተናጋሪ የሆነ ቤልጂየማዊ ዜጋ የሆነ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ሰራተኛ የተገኘ ሲሆን ስራውም መረጃ መሰብሰብ እንጅ አስተያየት መስጠት አለመሆኑን ገልጾ፣ ምንም ንግግር ሳያደርግ ወጥቷል።
Sunday, 8 February 2015
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዕድገት አለ ይላሉ፤ ተቃዋሚው እንደራሴ አይስማሙም
ዋሺንግተን ዲሲ - አዲስ አበባ—
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ፤ እንደራሴ ግርማ ሠይፉ፤ የኤርትራ ካርታ
የኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት በ2006 ዓ.ም በ10.3 ከመቶ እያደገ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ለፓርላማው ባቀረቡት ሪፖርት አስታውቀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቡት ሪፖርት በአጅጉ ያሣዘናቸው መሆኑን የገለፁት የተቃዋሚ ፓርቲው እንደራሴ ግርማ ሠይፉ ሪፖርቱ የሃገሪቱን እውነታ አያሣይም ብለዋል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ላይ የተጠናቀረውን አጭር ዘገባና የእንደራሴ ግርማ ሠይፉን አስተያየት የያዘውን ፋይል ያዳምጡ
http://amharic.voanews.com/audio/2632451.html
Saturday, 7 February 2015
ኢትዮጵያዊያን ዋሺንግተን ላይ በውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ደጅ ወጡ
ሕጋዊና ሕዝባዊ ድጋፍ ያላቸውን የፖለቲካ ፓርቲዎች ማፍረስ ሰላማዊ ትግሉን አደጋ ላይ ይጥላል ያሉ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ-ኢትዮጵያ ሠልፈኞች ዛሬ ዋሺንግተን ውስጥ በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ደጅ ላይ ተሰልፈው ድምፃቸውን አሰምተዋል፡፡
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሂደት ሀገርን የማይጠቅሙ አፈናዎች ቢበራከቱም ሰላማዊ ትግላችን ይቀጥላል ብለዋል ሠልፈኞቹ።
በዩናይትድ ስቴይትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ፊት ለፊት እጅግ የቀዘቀዘው የዋሽንግተን ዲሲ አየር ሳይበግራቸው የቆሙት ኢትዮጵያዊያን በዚህ የምርጫ ዓመት የኢትዮጵያ መንግሥት የዴሞክራሲ አፈናውን አጠናክሯል ሲሉ የተቃውሞ ድምፅ አሰምተዋል።
................ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ,-http://amharic.voanews.com/
Friday, 6 February 2015
5 የአየር ሃይል የጥበቃ አባላትና 2 ፓይለቶች ጠፉ
ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአየር ሃይል ምንጮች እንደገለጹት ከሁለት ሳምንት በፊት 5 የአየር ሃይል የጥበቃ አባላት እስከነ ሙሉ ትጥቃቸው እንዲሁም 2 ፓይለቶች ከድሬዳዋ አየር ሃይል ጠፍተዋል። የጥበቃ አባላቱም ሆነ ፓይለቶቹ ያሉበትን ለማወቅ የተደረገው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። ይህንን ተከትሎ ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ከመቶ አለቃ ማእረግ በላይ ያላቸውን አየር ሃይል አባላት ሰብስበው ግምገማ አካሂደው ነበር።
ጄ/ል ሳሞራ “የአየር ሃይል አባላት ለምን ይከዳሉ? አሁን ያላችሁትስ ምን ታስባላችሁ?” የሚል ጥያቄ ለተሰብሳቢው ያቀረቡ ሲሆን፣ የአየር ሃይል አባላቱም ከፍተኛ የሆነ የአስተዳደር በደል እንደሚደርስባቸው፣ ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ክፍያ እንደሚከፈላቸው፣ በመኖሪያ ቤት እጦት እንደሚሰቃዩ ገልጸዋል። መኮንኖቹ በርካታ ችግሮችን ዘርዝረው ያቀረቡ ቢሆንም፣ ጄ/ል ሳሞራ ችግሮችን ከመስማት ውጭ ምንም አይነት ምላሽ ሳይሰጡ ሄደዋል።
የአየር ሃይል አባላት ሞራል ( ስሜት) መዳከም ገዢው ፓርቲ በሩሲያ ቅጥር አብራሪዎች ላይ እምነቱን እንዲጥል አድርጎታል። የትግራይ ተወላጅ የሆኑት ሻምበል ሳሙኤል ግደይ እና ቴክኒሻን ብርሃን ግደይ ከመቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝ ጋር በመሆን ስርአቱን አናገለግልም ብለው ሄሊኮፕተር ይዘው መጥፋታቸው፣ የህወሃትን የዘር ፖለቲካ መሰረት እንዳናጋው ምንጮች ይገልጻሉ። ለወትሮው ይታመኑ የነበሩ የትግራይ ተወላጅ የአየር ሃይል አባላት ሳይቀሩ የሚታመኑ ሆነው ባለመገኘታቸው ፣ ባለስልጣናቱ አይናቸውን የውጭ ቅጥረኞች ላይ እያዞሩ ነው።
ስርዓቱን አናገለግልም ብለው የጠፉት የአየር ሃይል አባላት የተቃዋሚ ድርጅቶችን ተቀላቅለው እየታገሉ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የአፍሪካ መሪዎችም ሆነ የሌሎች አገራት መንግስታት ለስብሰባ ወደ አዲስ አበባ በሚመጡበት ጊዜ ለደህንነት ስራም ሆነ ለልዩ ጥበቃ የሚመደቡት የአንድ ብሄር ተወላጆች ናቸው በማለት የሌሎች ክልሎች የደህንነት አባላት ቅሬታ ማሰማታቸው ታውቋል። የ24ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ከተካሄደ በሁዋላ ለግምገማ ከተጠሩት ምድብተኛ የደህንነት ሰራተኞችና የጸጥታ አካላት መካከል አንዳንዶች፣ ” ለመሪዎችና ለእንግዶች ደህንነት የሚመደቡት ጠባቂዎች የአንድ አካባቢ ተወላጆች ብቻ መሆናቸው፣ “ስርአቱ የእናንተ አይደለም፣ አናምናችሁም” የሚል መልክት አለው በማለት በድፍረት ለገምጋሚዎች ተናግረዋል።
“በብሄራችን ምክንያት ተበድለናል” ያሉት የደህንነት ሰራተኞችና ጠባቂዎች፣ ደረሱብን ያሉዋቸውን በርካታ ችግሮች ዘርዝረው አቅረበዋል። ” በኢትዮጵያ ውስጥ አሸባሪዎች ራሳቸውን እያደራጁና መረባቸውን እየዘረጉ በመጡበት ሁኔታ የምናምነውን ሰው እንመድባለን” የሚል መልስ ግምገማውን ከሚመሩ መሪዎች የተሰጠ ሲሆን፣ ተሳታፊዎች በተሰጠው መልስ ማዘናቸውን በግምገማው የተሳተፉ የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
- source.- satenaw.com
አሜሪካ ፡ - "ኢትዮጵያ በስርዓቷ የወደቀች አገር ናት" ዶክመንተሪ ቪዲዮውን ይመልከቱ የአሜሪካ ፖሊሲ እና የኢትዮጵያ መንግስት ክሽፈት
ኢትዮጵያ መስቀለኛ መንገድ ላይ ናት::ውስጣዊ የፖለቲካ የማህበራዊ ኢኮኖሚ እና የሃይማኖት ችግሮኝ አጣብቂኝ ውስጥ ናቸው::በአሁን ወቅት ስልጣን ላይ የመጣውን መንስት ተከትሎ ጎሳን ያማከሉ ግጭቶች ተስፋፍተዋል::ይህ መንግስት በስልጣን ላይ ለ24 አመታት ቆይቷል::መሰረቱም በጎሰኝነት ላይ ሲሆን አስተዳደሩንም የያዙት አነስተኛ የሆኑ በጎሳቸው የተደረጁ የአንድ ብሄር ቡድን መሪዎች ናቸው::በሃገሪቱ የሚገኘውን እያንዳንዱን የመንግስት እና የግል ሴንተሮችን የተቆጣጠረው በራሱ ብሄር ተወላጆች እጅ ስር አድርጎ ነው:: ወታደሩ ደህንነቱ ሃይማኖቶች እና የኢኮኖሚ አውታሮች በትግራይ ብሄር ቡድን በሆነው በሕወሓት ቁጥጥር ስር ውለዋል:: የአሜሪካ መንግስት ያስጠናውን ጥናት ከፊል ሪፖርት ዝርዝር ከዚህ በሚከተለው ቭድዮ ይመልከቲት::
የዞን ዘጠኞችን ጉዳይ የሚያዩት መሃል ዳኛ በራሳቸው ፍቃድ ችሎቱን ለቀቁ
(ኢ.ኤም.ኤፍ) የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞችን ጉዳይ የሚመለከተው የልደታው ችሎት ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚሰጠው ውሳኔ ምን ሊሆን እንደሚችል በጉጉት ሲጠበቅ ነበር። በተለይም ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ የመሃል ዳኛው ስራቸውን በሚገባ እያከናወኑ ስላልሆነ፤ እንዲነሱላቸው ነበር በደብዳቤ የጠየቁት። ይህ ጥያቄ ለፍርድ ቤቱ ሲቀርብ ዳኞቹ ያልጠበቁት ነገር በመሆኑ፤ በመገረም ነበር ደብዳቤውን ደጋግመው የተመለከቱት። በሁኔታው ላይ ከተነጋገሩ በኋላ፤ የመሃል ዳኛውን ውሳኔ ለማሳወቅ ለሚቀጥለው ቀን ጠዋት ቀጠሮ ሰጥተው ነበር ችሎቱ የተጠናቀቀው።
ለፍርድ ቤቱ ያቀረቡት አቤቱታ የመጀመሪያ ገጽ (ምንጭ፡ ዞን ዘጠኝ ድረገጽ)ለፍርድ ቤቱ ያቀረቡት አቤቱታ 2ኛ ገጽ (ምንጭ፡ ዞን ዘጠኝ ድረገጽ
በሚቀጥለው ቀን የሆነው ነገር ብዙዎችን ያስገረመ ነበር። የመሃል ዳኛው አቶ ሸለመ በቀለ ውሳኔ ምን ሊሆን እንደሚችል ማንም አላወቀም። በሚቀጥለው ቀን ሦስቱ ጋዜጠኞችና ስድስቱ ጦማሪያን በልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ምድብ ችሎት ቀረቡ። ዞን ዘጠኞች ከአንድ ቀን በፊት፤ ማለትም በ26/05/2007 ዓ.ም. “የመሀል ዳኛው አቶ ሸለመ በቀለ ይቀየሩልን” ሲሉ በፅሁፍ ያቀረቡት አቤቱታ፤ በግራ እና በቀኝ ዳኛው ውድቅ የተደረገ መሆኑ ተገለጸ። በዚህም መሰረት “የመሃል ዳኛው ይነሱልን” ጥያቄ በድምጽ ብልጫ መውደቁ ታወቀ። ሆኖም የመሃል ዳኛው አቶ ሸለመ በቀለ በራሳቸው ፍቃድ ከመሃል ዳኝነት ያነሱ መሆናቸውን ገለጹ። “በራሴ ፈቃድ ከችሎቱ እራሴን አንስቻለሁ” ብለው በፍርድ ቤቱ ውስጥ ለተገኙት በሙሉ ነው ግልጽ ያደረጉት።
በፎቶው ላይ እንደሚታየው የመሃል ዳኛው የሉም። ጉዳዩን የተመለከቱት የግራ እና ቀኝ ዳኞች ናቸው። ተከሳሾች ቆመው ጉዳያቸውን ለፍርድ ቤት ሲያስረዱ ይታያል። ኤዶም ካሳዬ አግባብ ያልሆነው ኢፍትሃዊ ሂደት በመቃወም ጸጉሯን ተላጭታ ነበር የቀረበችው።
ይህም ሆኖ ጥያቄውን ያቀረቡት ጋዜጠኞች እያንዳንዳቸው 500 ብር ሊቀጡ እንደሚገባ ከተነገራቸው በኋላ፤ ለአሁኑ ግን በይቅርታ መታለፋቸውን ነው ፍርድ ቤቱ የገለጸው። ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ ከተከሳሾቹ መካከል አቤል ዋበላ እንደትላንት ከፍርድ ቤቱ ወደ ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት ሲወሰድ፤ ፖሊሶቹ እረስተው በእጁ ካቴና ሳያስገቡ ቀርተው ነበር። ያለካቴና ቅሊንጦ ከደረሰ በኋላ ግን የደረሰበትን ስቃይ ሲያስረዳ በፍርድ ቤቱ ውስጥ የተገኙት በሙሉ አዝነው ነበር። “ቅሊንጦ ስንደርስ እጄ ላይ ካቴና ስላልነበረ፤ የማረሚያ ቤቱ ሰራተኞች እየሰደቡ እና እያንገላቱ እጄን በውሻ ሰንሰለት አስረው ነው ያሳደሩኝ” በማለት እንባ እየተናነቀው ነበር የተናገረው። “ሌላው ቀርቶ ማዕከላዊ እያለሁ በደረሰብኝ ከፍተኛ ድብደባ ምክንያት አንድ ጆሮዬ በደንብ አይሰማም። በመሆኑም ለመስሚያ የሚያገለግለኝን የጆሮ ማዳመጫዬንም ወስደውብኛል” በማለት የደረሰበትን ግፍ እና በደል አስረድቷል።
ዳኛው… ለምን ይሄ እንደተደረገ የቅሊንጦ ማረሚያ ቤት ተወካይ ምላሽ እንዲሰጥ ብለው ሲጠይቁ፤ የቅሊንጦ አዛሪዎች ተወካይ አጥጋቢ መልስ መስጠት ሳይችል ቀርቷል። በመሆኑም በሚቀጥለው ቀጠሮ ማረሚያ ቤቱ ምላሹን በጽሁፍ እንዲያቀርብ አዘዋል።
zone9በመጨረሻም ሂደቱን በፎቶ ሊያነሳ የሞከረ አንድ ሰው በፖሊሶቹ ታስሮ ስልኩን ከወሰዱበት በኋላ፤ ወደ ቅሊንጦ እስር ቤት በሚሄደው የእስረኞች መኪና ውስጥ፤ በራሳቸው ስልጣን ለሰአታት ያህል ካሰሩት በኋላ ለቀውታል።
የዞን ዘጠኞች ቀጣይ ቀጠሮ ለየካቲት 11 ወይም ፌብሩዋሪ 18፣ 2015 ሲሆን፤ በሚቀጥለው ቀጠሮ ሲገኙ ለ21ኛ ግዜ ይሆናል ማለት ነው።
Thursday, 5 February 2015
መንግስት በፌስ ቡክና በሌሎች ማህበራዊ ሚዲያዎች ያሰማራቸው ሰዎች የተፈለገውን ውጤት ማምጣት አልቻሉም ተባለ።
ማህበራዊ ድረገጾች ላይ የመንግስትን መልካም ገጽታ ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊደርጉ ይችላሉ በሚል ተከታታይ ስልጠና ተሰጥቷቸው የነበሩት የህዝብ ግንኑነት ባለሙያዎች (ኮምኒኬተሮች) እና የመንግስት ባለስልጣናት፤የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አልቻሉም መባላቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖ ጠቆሙ፡፡
ለመንግስት የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎችና ለካድሬዎች በአቶ ሬድዋን ሁሴን በሚመራው የመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት አማካይነት ከአራት ወር በፊት በማህበራዊ ድረገጾች አጠቃቀምና በመንግስት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ላይ ተከታታይ ስልጠና መሰጠቱ ይታወቃል።
ሰልጣኞቹ ፌስቡክን ጨምሮ በተለያዩ ማህበራዊ ድረገጾች ላይ የመንግስትን አዎንታዊ ሚና አጉልተው በመጫወት የገጽታ ግንባታ ሥራ እንዲያከናውኑ የተሰማሩ ቢሆንም፤ እንደታሰበው ውጤት ሊያስገኙ አለመቻላቸው ተመልክቷል።
ጉዳዩን በቅርበት የኒያውቁ አካላት እንደሚሉት፦ውጤት ላለመገኘቱ ዋነኛው ምክንያት ብዙዎቹ “ኮምኒኬተሮች” በአቶ በረከት ስምኦን የሚኒስትርነት ዘመን ከየክልሉ በፖለቲካ ብቃት ብቻ ተመልምለው፣ በለብለብ ሥልጠና ወደሕዝብ ግንኙነት ሙያ የገቡከ መሆናቸው አኳያ ከፍተኛ የአቅም ችግር ስላለባቸው ነው።
ቀሪዎቹም በቤት አሰጣጥ፣ በደመወዝ ጭማሪና እና በመሳሰሉት ጉዳዮች በሚስተዋሉ አድሎአዊ የጥቅማጥቅም አሰጣጥ ያኮረፉ መሆናቸው ተገልጿል።
<<ኮምኒኬተሮቹ>> ከዛሬ አምስት ዓመት በፊት በየመስሪያ ቤቱ ሲመደቡ ፤ ቀደም ሲል በየመስሪያ ቤቶቹ ከነበሩ ብቃት ካላቸው የኮምኒኬሽን ባለሙያዎች አንዳንዶቹ ከቦታቸው እንዲነሱ ሲደረግ ፤የተቀሩት በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን ለመልቀቅ ተገደዋል፡፡
አብዛኛዎቹ<<ኮምኒኬተሮች>> ከተሰጣቸው ሥልጠና በሁዋላ እንደፌስቡክ ባሉ ማህበራዊ ድረገጾች ላይ የራሳቸውን ወይንም የድርጅታቸውን አካውንት ለመክፈት ሙከራ ከማድረግ በዘለለ ምንም ማከናወን ሳይችሉ መቅረታቸው፤ የአቶ ሬድዋንን ቢሮ ማበሳጨቱ ተጠቁሟል፡፡
በተለይ በፌስቡክ የሚሳተፈውን ዲያስፖራ እና የተቃውሞ ሃይሉን በአንድ ላይ በመጨፍለቅ «አክራሪ ሃይሎች» በሚል የፈረጀው ኢህአዴግ ፤ይህን ሃይል ቢቻል ጸጥ ለማሰኘት ካሰማራቸው ስልጣኞች ባሻገር ከ25 በላይ የሚሆኑ ሚኒስትሮች ሳ ማህበራዊ ድረገጾችንእንዲጠቀሙ ሲወተውት ቆይቷል።
ይሁንና እስካሁን በግልጽ የራሳቸው አካውንት ያላቸው ባለስልጣናት በጣት የሚቆጠሩ ከመሆናቸው አኳያ ለኢህአዴግ እንቅፋት የሆነውን ሃይል የሚገዳደሩ አለመሆናቸው ቢሮውንና ኢህአዴግን እንዳሳሰበው ከኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡
source,-ethsat.com
አቶ ሲሳይ ዘርፉ የጥፋተኝነት ውሳኔ ተላለፈበት
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ህዳር 27 እና 28/2007 ዓ.ም በ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ተዘጋጅቶ ለነበረው የአዳር ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ የቅስቀሳ በራሪ ወረቅት ሲበትን ለእስር የተዳረገው የሰማያዊ ፓርቲ አባል አቶ ሲሳይ ዘርፉ ዛሬ ጥር 28/2007 ዓ.ም የጥፋተኝነት ውሳኔ ተላፈበት፡፡
ታህሳስ 14/2007 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መናገሻ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ቆርቦ የነበረው አቶ ሲሳይ ዘርፉ ‹‹…‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ› ለመላው ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ሁሉ….ተብሎ የተጻፈበት በራሪ ወረቀቶች ለህብረተሰቡ ሲያከፋፍል እጅ ከፈንጅ በመያዙ በፈጸመው የሐሰት ወሬን በማውራት ህዝቡን ማነሳሳት ወንጀል…›› በሚል በፌደራል አቃቤ ህግ ለቀረበበት ክስ ያቀረበው የክስ መቃወሚያ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ መደረጉ ይታወሳል፡፡
ከዚህም ባሻገር አቶ ሲሳይ ዘርፉ ጥር 7/2007 ዓ.ም የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርና ም/ሊቀመንበር የሆኑትን ኢ/ር ይልቃል ጌትነትና አቶ ስለሺ ፈይሳ እንዲሁም የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ህብረት (ኦህዴህ) ሊቀመንበር አቶ ግርማ በቀለን በመከላከያ ምስክርነት አቅርቦ የነበር ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ‹‹ምስክሮቹ ከወንጀል ድርጊቱ ጋር ቀጥተኛ የሆነ ምስክርነት ሳይሆን የራሳቸውን የፖለቲካ አመለካከት ሚዛናዊነት በጎደለው መልኩ ነው ያቀረቡት፡፡›› በሚል ምስክሮቹ የሰጡትን የምስክርነት ቃል ውድቅ አድርጓል፡፡
አቃቤ ህግም በተሰጠው የጥፋት ውሳኔ ላይ ‹‹ተከሰሽ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ 82(ሀ) 1/ መሰረት ማቅለያው ታይቶለት ከዚህ ቀደም የወንጀል ድርጊት ያልፈጸመ ስለሆነ የምንጠይቀው የቅጣት ማክበጃ የለንም፡፡ ሆኖም ግን በሰራው የወንጀል ድርጊት የመጨረሻው ጣሪያ ውሳኔ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን፡፡›› ብሏል፡፡ ፍርድ ቤቱ ለካቲት 3/2007 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት በመናገሻ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡
አቶ ሲሳይ ዘርፉ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለበት ዕለት ጀምሮ ዋስትናው ተነፍጎ ቀደም ብሎ በፖሊስ ጣቢያና አሁን ደግሞ ቂሊንጦ እስር ቤት በእስር ላይ ይገኛል፡፡
Wednesday, 4 February 2015
ጸጉሯን ተላጭታ ፍርድ ቤት ቀረበች የዞን ዘጠኟ ጋዜጠኛ ኤዶም
የዞን ዘጠኟ ጋዜጠኛ ኤዶም ጸጉሯን ተላጭታ ፍርድ ቤት ቀረበች – “የእምነት ክህደት ቃላችንን ከመስጠታችን በፊት ዳኛው ይነሱልን” – ዞን ዘጠኞች
>በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞች ሰብሳቢ ዳኛው ከችሎት እንዲነሱ ጠየቁ፡፡
ጥር 26/2007 ዓ.ም ለ17ኛ ጊዜ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ልደታ ምድብ የቀረቡት ጦማርያኑና ጋዜጠኞቹ የችሎቱ ሰብሳቢ ዳኛ የሆኑት አቶ ሸለመ በቀለ ‹‹የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብታችንን አላስከበሩልንም›› በሚል ከችሎት እንዲነሱ በጽሑፍ አቤቱታ አቅርበዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ የተሰየመው ተሻሽሎ ቀርቧል በተባለው የአቃቤ ህግ ክስ ላይ የተከሳሾችን የእምነት ክህደት ቃል ለመስማት እንደነበር ዳኞቹ ቢናገሩም፣ ተከሳሾች አቤቱታ እንዳላቸው በመግለጽ የእምነት ክህደት ቃል ለመስጠት ዝግጁዎች አለመሆናቸውን ለችሎቱ ማስረዳት ችለዋል፡፡
ተከሳሾች ‹‹እኛ በሰብሳቢ ዳኛው ላይ አቤቱታ አለን፤ ፍርድ ቤቱ የራሱን ውሳኔ እንኳ አላከበረም፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆነን የእምነት ክህደት ቃላችንን ለመስጠት ዝግጁዎች አይደለንም›› በሚል ፍርድ ቤቱ አቤቱታቸውን እንዲቀበል ጠይቀዋል፡፡
ዳኛ ሸለመ በቀለ ‹‹ፍርድ ቤቱ ቃሉን አላከበረም›› በሚለው ጉዳይ ላይ መልስ ሲሰጡ ‹‹የእኛን ውሳኔ የማትቀበሉ ከሆነ ጉዳዩን በይግባኝ እንዲታይ ማድረግ ይቻላል›› ብለዋል፡፡
‹‹ላለፉት ስድስት ወራት በነበረው የክርክሩ ሂደት የችሎቱ ሰብሳቢ ዳኛ አቶ ሸለመ በቀለ ሂደቱን በአግባቡ በመምራት የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብታችንን አላስጠበቁልንም፡፡ በተለያየ ጊዜም ሐሳባችን ለመግለጽ ስንሞክር ክልከላ አድርገውብናል፡፡ አሁን ደግሞ ችሎቱ ራሱ የሰጠውን ትዕዛዝ ራሱ ሽሮ ፈጽሞ ልንረዳው በማንችለውና የመከላከል መብታችንን በሚያጣብብ የክስ ሁኔታ ክርክሩን እንድንቀጥል ሲበየንብን የችሎቱ ሰብሳቢ ወሳኝ ሚና ነበራቸው›› ሲሉ ተከሳሾች በሰብሳቢ ዳኛው ላይ ቅሬታቸውን በአቤቱታቸው ገልጸዋል፡፡
ፍርድ ቤቱም የችሎቱ ሰብሳቢ ዳኛ አቶ ሸለመ በቀለ ከችሎት እንዲነሱ የሚጠይቀውን አቤቱታ አይቶ ነገ ብይን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
............SOURCE,- http://www.zehabesha.com/
መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ እስር ቤት ውስጥ በደረሰባቸው ችግር ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ እኚህ ነበሩ
የህዳር 27/28 የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የጠራው የአዳር ሰልፍ ወቅት ተይዘው በደረሰባቸው ከፍተኛ ድብደባ እና ለሶስት ቀን የስኳር በሽታ መድሃኒት እንዳይገባላቸው በመከልከላቸው ለህመም የተዳረጉት የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) ምክትል ፀኃፊ መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ ከእስር ከተፈቱበት ጊዜ ጀምሮ ለሁለት ወር ሆስፒታል ከቆዩ በኋላ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ በአዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው ሲሆን ለአምስት ቀናት ቀዝቃዛና ጨለማ ቤት ውስጥ ታስረው ቆይተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ ይዘውት የነበረውን የስኳር በሽታ መድሃኒታቸውን በመቀማታቸው፣ እንዳይገባላቸው በመከልከላቸውና በወቅቱም ህክምናም ባለማግኘታቸው ለከፍተኛ ህመም በመዳረጋቸው ለሁለት ወር ያህል ዘውዲቱ ሆስፒታል ቆይተዋል፡፡
መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ እስር ቤት እያሉ በደረሰባቸው ችግር ምክንያት ዘውዲቱ ሆስፒታል ከገቡበት ታህሳስ 4/2007 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ ህመም እየተሰቃዩ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የመቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ የቀብር ስነስርዓት ዛሬ ጥር 27/2007 ዓ.ም በቦሌ ሚካኤል እንደሚፈጸም ለማወቅ ተችሏል፡፡
source,-http://ethioforum.org/amharic/
Tuesday, 3 February 2015
35 ሰዎች ቀይ ባህር ውስጥ ጠፉ * የ9 ኢትዮጵያውያንን ሰውነት አግኝተዋል
35 ሰዎች ቀይ ባህር ውስጥ ጠፉ * የየመን ነብስ አድን ሰራተኞች የ9 ኢትዮጵያውያንን ሰውነት አግኝተዋል
ዘ-ሐበሻ) ዜግነታቸው ከኢትዮጵያ ሶማሊያና አካባቢው ሃገራት እንደሆነ የሚገመት 35 አፍሪካውያን ቀይ ባህር ውስጥ ይጓዙበት የነበረችው ትንሽዬ ጀልባ ሰጥማ የት እንደደረሱ ሊታወቅ አለመቻሉን የየመን ባለስልጣናት አስታወቁ::
በደቡባማው የየመን ክፍል ቲያዝ አቅራቢያ በሚገኘው የቀይባህር ውስጥ ሰጥመዋል ስለተባሉት አፍሪካውያን የየመኑ ባለስልጣን ጀነራል ሰኢድ ስባሪ ሲናገሩ እነዚህ ሰደተኞች በባህር ላይ ይጓዙ የነበረው 49 ሆነው ሲሆን በነበረው መጥፎ አየር የተነሳ ሊሰጥሙ ችለዋል:: እንደ ጀነራሉ ገለጻ የየመን መንግስት የ13 ሰዎችን ሰውነት ያተረፈ ሲሆን 9ኙ የኢትዮጵያውያን እንዲሁም 5ቱ የሶማሊያውያን ነው ተብሏል::
እንዲህ ያለው አሰቃቂ አደጋ በየመን አካባቢ ሲደርስ በ6 ወር ጊዜያት ውስጥ ለ3ኛ ጊዜ ሲሆን ባለፈው ዲሴምበር 12 የየመን መንግስት የ24 ኢትዮጵያውያንን አስከሬን ከባህር እንዳወጣ; እንዲሁም በጁላይ 12 70 ኢትዮጵያውያን እንዲሁ በቀይ ባህር ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም::
እንደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት መግለጫ በዚሁ በቀይባህር በኩል ተሻገረው ወደ የመን ከሚሄዱ አፍሪክውያን መካከል በሺህዎች የሚቆጠሩት ሕይወታቸው በአንድ ዓመት ውስጥ ያልፋል::
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/
ሰበር ዜና – የአንድነት አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ
(ሰማያዊ ፓርቲ) ብሄራዊ ምርጫ ቦርድና ኢህአዴግ በወሰኑብን ፖለቲካዊ ውሳኔ ምክንያት አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ተነጥቀናል ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት› በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን አስታወቁ፡፡
በእነ በላይ ፍቃዱ አመራርነት አንድነት ፓርቲን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ሲመሩ የነበሩ አመራሮች ዛሬ ጥር 26 ቀን 2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት ከቀድሞ ፓርቲያቸው አንድነት ጋር የፕሮግራምም ሆነ የስትራቴጂ ተመሳሳይነት ወዳለው ሰማያዊ ፓርቲ ተቀላቅለው ሰላማዊ ትግላቸውን ለመቀጠል መወሰናቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
መግለጫውን የ‹ቀድሞው አንድነት ፓርቲ› አፈ ጉባዔ የነበሩት አቶ አበበ አካሉ፣ ምክትል አፈ ጉባዔው አቶ ፀጋዬ አላምረው፣ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ነገሰ ተፋረደኝ እንዲሁም የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ሌሎችን በመወከል ሰጥተዋል፡፡
‹‹የምናምነው በሰላማዊ ትግል ብቻ ነው፡፡ ይህን ሰላማዊ ትግል ለመምራት ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ብቁ ነው ብለን በማመን ፓርቲውን ተቀላቅለናል›› ብለዋል በመግለጫው ላይ የተወከሉት አዲሶቹ የሰማያዊ አባላት፡፡
በዚህ መሰረትም በርከት ያሉ አመራሮችና አባላት በይፋ የሰማያዊ ፓርቲ የአባልነት ፎርም ሞልተዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአንድነት አባላት ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን አስመልክቶ መግለጫ ለመስጠት ወደ ሰማያዊ ቢሮ ባቀኑበት ወቅት ፖሊስ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ድረስ በመግባት ‹‹በሰማያዊ ስም መግለጫ የሚሰጡ አካላት እንዳሉ ሰለሰማን ነው›› በሚል ለፓርቲው አመራሮች ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡
..........................
source,-http://ecadforum.com/
Monday, 2 February 2015
አባዱላ ገመዳ በሚኒሶታ ቅሌትን ተከናነቡ
አባዱላ ገመዳ በሚኒሶታ ቅሌትን ተከናነቡ (በሬስቶራንት ውስጥ የደረሰባቸውን የውርደት ቪድዮ ይዘናል)
aba dula
(ዘ-ሐበሻ) በምሽትና በድብቅ ሀሙስ ምሽት ሚኒሶታ የገቡት የሕወሓት ተላላኪው ባለስልጣን አባዱላ ገመዳ በሚኒሶታ ቅሌትን መከናነብ የጀመሩት ገና ከአውሮፕላን ከወረዱ ጀምሮ ነበር::
አባዱላ የሕወሓት ተላላኪ ሆነው የኢትዮጵያን እመራታለሁ እያሉ ከኤርፖርት የተቀበሏቸው ጥቂት ሶማሊያውያን የታክሲ ሾፌሮች ናቸው:: እነዚህ የሱማሊያ ታክሲ ሾፌሮች አባዱላን ከተቀበሉ በኋላ ብሎሚንገተን በተሰኘው የሚኒሶታ ከተማ ሂልተን ሆቴል ያሳረፏቸው ሲሆን እንደዚህ ቀደሙ የወያኔ ተላላኪዎች ሲመጡ ፖስተር ተለጥፎ ስብሰባ እንደሚጠራው ለአባዱላ የወያኔ ተላላኪዎች ያደረጉት ነገር የለም:: ይልቁንስ በቴክስት መልክት ብቻ በስልክ የወያኔ ኔትወርኮች ብቻ እንዲጠራሩ የተደረገና ሌላው ሕዝብ የአባዱላን ስብሰባ እንዳይሰማ ለማድረግ ጥረት ቢደረግም ይህ ቴክስት መልዕክት ለኢትዮጵያን ደረሰ::
ኢትዮጵያውያኑ ልክ እንደሕወሓት ተላላኪዎች ድምፃቸውን ሳያሰሙ በቴክስት መልዕክት የተጠራሩ ሲሆን ስብሰባው የሚደረግበት ሂልተን ሆቴል ተገኝተዋል:: አባዱላ ገመዳ ከአንዲት ሴት ጋር ሁለተኛ ፎቅ ላይ ቁጭ ብለው ወደታች በአንደኛው ፎቅ በኩል የሚገቡትን ሰው እየተመለከቱ; አጠገባቸው ያለችው የትግራይ ተወላጅ የሆነች ሴት የሰውን ማንነት የምትነግር ይመስል ለባለስልጣኑ ትጠቁማለች::
በዚህ መሃል የዘ-ሐበሻ አዘጋጆችም ሲገቡ ሴትየዋ ለአባዱላ በጥቆማ ስታሳይ የዘ-ሐበሻ አዘጋጆች ተመልክተዋል:: የዘ-ሐበሻ አዘጋጆች ወደ ስብሰባው ሊገቡ ሲሉ እንደተለመደው የተከለከሉ ሲሆን ስብሰባውን ያዘጋጀው አካል ከ30 በላይ የሚቆጠሩ ፖሊሶችን በመቅጠር ተቃዋሚ የሆኑ ሰዎች እንዳይገቡ ተከልክለዋል:: አንድ ፖሊስን በሚኒሶታ ለአንድ ዝግጅት በሰዓት መንግስት ከሚከፍለው በተጨማሪ ዝግጅት አዘጋጁ ከ$50 ዶላር ያላነሰ የሚከፍል ሲሆን የሕወሓት መንግስት ለነዚህ የአሜሪካ ፖሊሶች ለ6 ሰዓታት ለ እያንዳዳቸው $300 ዶላር በአጠቃላይም ለፖሊስ 9 ሺህ ዶላር አውጥቷል:: ይህም በኢትዮጵያ ብር ሲመነዝር 180 ሺህ ብር መሆኑ ነው:: ለአዳራሽ በትንሹ ከ2 ሺህ ዶላር በላይ, ለሶማሌ ታክሲ ሾፌሮች በሰዓት ከ60 ዶላር በላይ እንዲሁም ለአባዱላ እና ለተላላኪዎቻቸው የሆቴል አዳር ከ150 ዶላር በላይ የወጣበት ይኸው የሚኒሶታ ስብሰባ ካለስኬት የተጠናቀቀ ሲሆን በስበባው የተገኘው ሕዝብም ከ45 ሰው እንደማይበልጥ በውስጥ ጉዳዩን እንዲከታተሉ የላክናቸው ምንጮች አስታውቀዋል::
የሕወሃት መንግስት ተላላኪው አባዱላ ገመዳ በሚኒሶታ ስብሰባ እንዲያደርግ ግማሽ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር ያጠፋ ሲሆን ያተረፈው ጥፋትን ብቻ ሳይሆን አባዱላ ገመዳ በሄዱበት ቦታ ሁሉ ስድበንም ጭምር ነው:: በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን በሂልተን ሆቴልና በተለያዩ አባዱላ በሄዱባቸው የኢትዮጵያ ሬስቶራንቶች በመገኘት አባዱላን በሰብ አዊ መብት ረገጣ, በአፋኝነት, በአምባገነንነት, በሙስና እና በግድያ ወንጀሎች ሲናገሯቸውና በርሳቸው ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ሲያሰሙባቸው ውለዋል:: በአጠቃላይ የሕወሓት መንግስት የዲያስፖራ ሳምንት በኦሮሚያ አከብራለሁ ብሎ ስብሰባ የጠራበት የአባዱላ ስብሰባ ከትርፉ ኪሳራው አመዝኗል:: ኢትዮጵያውያኑም በሚኒሶታ በተቃውሞ ሲያሸብሩት ውለዋል::
አባዱላ ገመዳ ዛሬ በሚኒሶታ የደረሰባቸው ቅሌት ነገ በሲያትል እንደሚደገም ይጠበቃል:: በሲያትል ያሉ ኢትዮጵያውያን የአባዱላን የህወሃት ተልኮ ለማክሸፍ እየተጠባበቁ እንደሆነ የደረሰን መረጃ ያመለክታል:: አባዱላ በሬስቶራንት ውስጥ የደረሰባቸውን የተቃውሞ ውርደት ቭዲዮ ይመልከቱ::
- .....See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/38630#sthash.EKn2EcYu.xbNHJn76.dpuf
Saturday, 31 January 2015
ህወሃት በዘረፈውና በሚዘርፈው ሃብት ተጠቅሞ ለወዳጆቹ የሚያኮራ፣
ህወሃት በዘረፈውና በሚዘርፈው ሃብት ተጠቅሞ ለወዳጆቹ የሚያኮራ፣ ትውልድ ለሚላቸው የሚበጅ ተግባራት እያከናወነ እንደሆነ ይነግረናል፤ ይነግሩናል። ውስን ባለሥልጣናትና አበሮቻችው በሃብት ተመንድገዋል። በንዋይ ሰከረው የሚያደርጉት እስኪጠፋቸው ናጥጠዋል። የት ጋር አንደሚያበቃ ባይታወቅም፣ የተደሰቱ፣ የተከፉ፣ የተናቁ፣ የተሰረቁ፣ የሚሰረቁ፣ እየሰረቁ ያሉ፣ የተትረፈረፈላቸው፣ በስማቸው የሚነገድባቸው፣ ባሪያዎችና ባንዳዎች፣ ቀን የሚጠብቁ፣ ጥርሳቸውን የነከሱ፣ … ወዘተ “አብረው” አሉ፡፡
ዘመን፣ ወራትና ቀናት ቅዠትን በመሰሉበት ዓለም፣ ቁራሽ ለሚሞላው ከርስ ራሳቸውንና ማንነታቸውን፣ ከዚያም አልፎ የትም የማይደበቁትን ኅሊናቸውን ያቆሸሹ፣ የአገር “እንግዴ ልጆች” ወይም “ውርጃዎች” ለህወሃት የማከሰምና የመግደል ሴራ ተላላኪ ሆነው የህዝብን ክብር ሰልበው ረክሰው ያረከሳሉ። ከዚህም በላይ ነገ እንደ ውዳቂ ላንቲካ መጣላቸውን እያወቁ፣ አሽከርነት፣ ከሃዲነት፣ ውርደት፣ መለያቸው እንዲሆን መርጠው ተሳቅቀው ይኖራሉ። እነሱን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ባመነበት መንገድ እንዲጓዝ ለመታገል የሚውተረተሩትን ተኩላ ሆነው ያስበሏቸዋል።
ቅንጅትን በሉት። ቅንጅትን አሳረዱት። ተቀራመቱተ። የውስጥ ችግሩ እንዳለ ሆኖ እነርሱ ግን ዕጣ መድበው ተጣጣሉብት። አየለ ጫሚሶና ባልደረቦቻቸው “የክህደት ዋንጫ” ተሞላላቸው። ከዚያም ተጣሉ።
አሁን “ምርጫ” ደርሷል፤ ድንጋጤ ጨምሯል፤ የሕዝብ ሱናሚ አስፈርቷል፤ የህንጻውና የመንገዱ ሁኔታ አልበቃም፤ የሰዉ ህይወት ከመቅለሉ የተነሳ ለሚዛን አልበቃ ባለበት አገር ህይወቱ “በቀላል ባቡር ሊቀልል” ሽር ጉድ ይባላል፤ “ሥራ ላይ ነን፤ ምርጫ ደርሷላ”፤ አስተናጋጇ ህወሃት በለመደችው መንገድ ልታባብል ብዙ ትጥራለች፤ በየማዕዘኑም እያደባች ነው፤ እስከ “ምርጫ” ቤቷን አሳምራ ቄጠማ ጎዝጉዛ፣ ፈንዲሻ ነስንሳ፣ ዕጣኗን አጫጭሳ “እንኮምር” እያለች ነው፡፡ ግን አልበቃትም፤ አላመነችም፤ ተጠራጥራለች፤ ተጨንቃለች፤ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን በተለይም አንድነትን ለማጥፋት “ቡና ጠጡ” በማለት የሚላላኩላት የቦርዱ “ምሁራን” ላይ ታች እያሉ ነው። ኃላፊው ለምን ይህንን የተላላኪነት ሥራ እንደፈለጉት ባይታወቁም የቦርዱ አሽከርካሪ ምክትላቸው ግን “የዜግነት” ድርሻውን እየተወጣ ነው፡፡ “ለወገን ደራሹ ወገን” አይደል የሚባለው! ስለዚህ ህወሃት የሰፈረውን “የሚያገለማ ጽዋ” ለመጋት ርኩቻው ደርቷል። ፕሮፌሰርነት ከሚሰጠው ክብር ይልቅ “ተላላኪነት” ኩራት ሆነ
በአገራችን ሶስት ዓይነት ባርነት እንዳለ ይነገራል፡፡ የእነዚህ ባሪያዎች (ባንዶች) ማንነት ገፍቶ የሚወጣው “ምርጫ” በደረሰ ጊዜ ነው፡፡ አንደኛውና የመጀመሪያው ባሪያ “ምርጫ ቦርድ” የሚባለውና ሌሎች መሰል “የተቋም ባሮች” ናቸው፡፡ ሁለተኛው ባሪያ ምርጫ ቦርድን እና ተመሳሳይ ተቋማትን የሚመሩ አመራሮች ናቸው፡፡ ሦስተኞቹ ባሮች ደግሞ ህዝባቸውን ለንዋይ ሲሉ የሚሸጡ አገልጋዮች ናቸው፡፡ በሌላ ቋንቋ ህወሃት የጠፈጠፋቸው፣ ያቦካቸው፣ የሚነዳቸው፣ ሲፈልግ አዋርዶ የሚያባርራቸው ናቸው፡፡ የዘመንና የትውልድ ሁሉ ተጠያቂ ባንዳዎች!
ሰሞኑን ምርጫ ቦርድ የባርነቱን ዘመን ለማራዘም በለመደ እጁ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ላይ “አብዮታዊ ዴሞክራሲ” ጡጫ ለማሳረፍ፣ ለመሰንጠቅ፣ ለማክሰምና ለማፍረስ ደፋ ቀና እያለ ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል ቅንጅትን በማፍረስ ታማኝ ሎሌነቱን እንዳስመሰከረ ሁሉ አሁንም ለህዝብ የእንግዴ ልጅነቱን ለህወሃት/ኢህአዴግ ደግሞ ታማኝ አሽከርነቱን ለማረጋገጥ እየተባ ይገኛል፡፡
እኛም እንደ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የባንዳዎችን ጥርቅም እናወግዛለን፡፡ ታሪክና ትውልድም ይህንን እንዳይረሱት እናሳስባለን፤ እንመዘግባለን፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ የሚዘርፉትን፣ እየዘረፉ ያሉትን፣ የተዘረፉትን፣ እየተዘረፉ ያሉትን፣ ዘርፈው የሚያደርጉት የጠፋባቸውን፣ በሃብት የናወዙትን፣ በደም የተጨማለቁትን፣ የራባቸውን፣ ምርጫ ቦርድን፣ የኢህአዴግን ሎሌዎች፣ አሽከሮች፣ ሁሉ ይዛ እየነጎደች ነው፡፡ የጥጋቡም የግፉም ማብቂያ መቼ እንደሆነ ባይታወቅም የከፋቸውና ጥርሳቸውን የነከሱ እንዳሉ ከበቂ በላይ ማስረጃ አለን፡፡ ንጹህ አገር ወዳዶችና እኛም ጎልጉሎች ያንን ቀን አንናፍቀውም፡፡ ባንዶች ግን ይህንን ቀን የማስቀረት አቅም አላችሁና ወደ ኅሊናችሁ ተመለሱ፡፡ ህዝብ ይምረጣቸው ወይም ይጥላቸው አንድነትንም ሆነ ሌሎቹን የተቀናቃኝ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ከራሳቸው ችግር ጋር ለህዝብ ውሳኔ ብትተዋቸው ይሻል ነበር፡፡ ነገርግን ውሻ ወደ ትፋቱ እንደሚመለስ እናንተም ዳግመኛ ባንዳነታችሁን አስመሰከራችሁ፤ ባርነታችሁንም ቀጠላችሁበት፡፡
...........................source.-www.goolgule.com
Friday, 30 January 2015
ሼክ አላሙዲን ከባለስልጣናት ጋር ወደ 30 የሚጠጉትንና እጅግ አትራፊ የሆኑ ድርጅቶችን በርካሽ ዋጋ ወደ ግል እንዲያዞሩ ረድቷቸዋል ተባለ
. . ሼክ ሙሃመድ አላሙዲን ከባለስልጣናት ጋር ባላቸው ቀረቤታ የህዝብ ሃብት የሆኑ ኩባንያዎችን ወደ ግል እንዲያዞሩ ረድቷቸዋል ተባለ iየፕራይቬታይዜሽንና የመንግስት ልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ የመንግስት ልማት ድርጅቶችን መሸጥ ከጀመረበት ከ1997 ዓ.ም እስከ 2006 ዓ.ም ድረስ ባሉት ጊዜያት ከሸጣቸው 370 ድርጅቶች መካከል ሼህ አልአሙዲ ወደ 30 የሚጠጉትንና እጅግ አትራፊ የሆኑ ድርጅቶችን በርካሽ ዋጋ መሰብሰብ መቻላቸው ስርአቱ ለተዘፈቀበት ሙስና ማሳያ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ገልጸዋል።
ሼሁ የለገደንቢን ወርቅ ማዕድን በአሁኑ ወቅት ሚድሮክ ወርቅ ማዕድን ኩባንያ እየተባለ የሚታወቀውን በ1989 ዓ.ም በብር 1 ቢሊዮን 128 ሚሊዮን 543 ሺ ከ28 ሳንቲም በመግዛት በእጃቸው አስገብተዋል፡፡ ኩባንያው በ2006 በጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሚሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ በማስገባቱ ምክንያት ባለፈው ወር የኢትዮጽያ ንግድ ባንክ ሸልሞታል፡፡ ለኢህአዴግ ከፍተኛ ጥቂት አመራሮች ባላቸው ቅርበት የሚታወቁት ሼህ አልአሙዲ ባለፉት 17 ዓመታት
በፕራይቬታይዜሽን ስም በይስሙላ በሚወጡ ጨረታዎች ወሳኝ የሆኑ ኢንዱስትሪዎችንና የእርሻ ድርጅቶችን በርካሽ ዋጋ በእጃቸው ማስገባት እንደቻሉ መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ከነዚህ ድርጅቶች መካከል በቀድሞ ስማቸው የሚታወቁትን ፔፕሲ ኮላ ፋብሪካዎች፣ ድል ቀለም ፋብሪካ ፣ዋንዛ የእንጨት ውጤቶች ድርጅት፣ ዪኒቨርሳል እና አዋሽ ቆዳ ሁለት ፋብሪካዎች፣ ጎንደር፣ ድሬዳዋ እና ኮምቦልቻ ሶስት የሥጋ ውጤቶች ፋብሪካዎች፣ ለገደንቢ ወርቅ ፋብሪካ፣ አዲስ ጎማ (ሆራይዘን) ፋብሪካ፣ ደብረዘይት ሆራ ራስሆቴል፣ ውሽውሽ ጉመሮ ሻይ ልማትና ገበያ ድርጅት ፣ጎጃም፣ጎንደር፣የላይኛውና የታችኛው ብር ሸለቆ እርሻ ልማት፣ጎጀብ እርሻ ልማት፣ ጥቁር አባይ ጫማ ፋብሪካ እና የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡
ሼህ አላሙዲን በተለይ ደብረዘይት ሆራ ራስ ሆቴልን እጅግ ርካሽ በሚባል በ9 ሚሊየን ብር በ1990 ዓ.ም ቢገዙም እስከአሁን ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ አጥረው ከማስቀመጥ ውጪ ሊሰሩበት አልቻሉም፡፡
ሼህ አልአሙዲን በተለይ እንደእነአቶ በረከት ስምኦን የመሳሰሉ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር በመቀራረብ የግልና የቤተሰቦቻቸውን የህክምናና መዝናኛ እንዲሁም አንዳንድ ወጪዎችን በመሸፈን፣ እንደቤትና መኪና የመሳሰሉ ውድ ስጦታዎችን በመስጠት ግልጽ የሆነ ሙስና እንደሚፈጽሙ፣ለዚህ ወሮታቸውም የጠየቁትን የህዝብ ሐብት ያለአንዳች ችግር እንዲወስዱ እንደሚደረግ ምንቾች ገልጸዋል። ሼክ አላሙዲ ከ10 አመት በፊት ኢህአዴግን በመደገፍ በምርጫ ቅስቀሳ መሳተፋቸው ይታወቃል።
- See more at: http://satenaw.com/amharic/
የአንድነትና የመኢአድ ቢሮ በፖሊስ ተከቧል
የአንድነት ለፍትሕና ዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) ቢሮ በፖሊስና በደህንነት መከበቡን አቶ አስራት አብርሃ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ቢሮው በደህንነትና በፖሊስ በመከበቡ አባላት መውጣትና መግባት እንደማይችሉ የገለጹት አቶ አስራት ‹‹ውጭ ያለነው ወደ ውስጥ እንዳንገባ ተከልክለናል፡፡ ውስጥ ያሉትም መውጣት አይችሉም፡፡›› ብለዋል፡፡ የአንድነት አመራሮችና አባላት እንዳይወጡና እንዳይገቡ የከለከሉት ደህንነትና ፖሊሶች የከበባውን ምክንያት እንደማይናገሩ አቶ አስራት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ቢሮው በፖሊስና በደህንነቶች በመከበቡ አመራሮችና አባላቱ ወደ ውስጥ መግባትም ሆነ ወደ ውጭ መውጣት እንደማይችሉ ተግልጾአል፡፡
(ኢ.ኤም.ኤፍ) በቅርቡ ምርጫ ቦርድ – የአንድነት እና መኢአድ ፓርቲን መሰረዙን ገልጿል። ምርጫ ቦርድ ይህን ያደረገበት ምክንያት ለብዙዎች ግልጽ ነው። እነዚህ ሁለት ትላልቅ ፓርቲዎች ከኢህአዴግ ጋር ከጥቂት ወራት በኋላ ለህዝባዊ ምርጫ ይቀርባሉ። ምርጫውን ከተሳተፉ ደግሞ… ፓርቲዎቹ ለኢህአዴግ ስጋት ናቸው። በዚህም ምክንያት ምርጫ ቦርዱ የተለያዩ ምክንያቶች እየሰጠ ከከረመ በኋላ ሁለቱን ፓርቲዎች ከምርጫው በፊት ከጨዋታው እንዲወጡ አድርጓል።
ይህ ከመሆኑ በፊት ግን በተለይ አንድነት ፓርቲ፤ ከፓርላማው አፈ ጉባኤ ጀምሮ እስከ ምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ድረስ የተጻጻፋቸውን ደብዳቤዎች ኢ.ኤም.ኤፍ አግኝቷቸዋል። እነዚህ ደብዳቤዎች በማንበብ ወቅታዊውን የአገራችንን የምርጫ ሂደትት መገንዘብ ይቻላል። ከምንም በላይ ደግሞ ይህ ቀን ሲያልፍ ጥፋተኞች በህግ እና በታሪክ ፊት ማንነታቸው ይጋለጣል። እርስዎም ለታሪክ ምስክር ይሆንዎት ዘንድ እነዚህን መረጃዎች መጫን ወይም ለሌሎች ማካፈል ይችላሉ።
39ኙን ገጽ የደብዳቤ ልውውጥ ለማንበብ ወይም ለማውረድ ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ።
..አንድነት እና ምርጫ ቦርድ ያደረጉት የደብዳቤ ልውውጦች
.......................http://ethioforum.org/amharic/wp-
Thursday, 29 January 2015
ለጋዜጠኞች ጥያቄ ዕድል የነፈገው ‹‹ታሪካዊው የምርጫ ››
.ለጋዜጠኞች ጥያቄ ዕድል የነፈገው ‹‹ታሪካዊው›› የዛሬ የምርጫ ቦርድ ጋዜጣዊ መግለጫ (ኤልያስ ገብሩ ጎዳና )
በዛሬው ዕለት ጥር 21 ቀን 2007 ዓ.ም ከቀኑ አስር ሰዓት ላይ በሂልተን ሆቴል ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲንና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)ን በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር፡፡ በመግለጫውም የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና እና የቦርዱ ጸሐፊና የጽ/ቤቱ ዋና ኃላፊ አቶ ነጋ ዱሬሳ ተገኝተው የመግለጫውን ዓላማ እና ስምንት ገጽ የሆነውን መግለጫ አንብበዋል፡፡
‹‹የአንድነት የቦርድ ዕውቅና ያለው መተዳዳሪያ ደንብ የ2004 ዓ.ም ስለመሆኑ፣ ቦርዱ የፓርቲውን እንቅስቃሴ ከዚሁ የቦርድ ዕውቅና ካለው ደንብ አንጻር ሲመረምር እንደቆየና አሁንም ከዚሁ አኳያ የመረመረ ስለመሆኑ ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል›› የሚለው መግለጫ፣ አሁን ተመርጠናል በሚሉት በእነ አቶ በላይ ፈቃዱ ቡድን በኩል የተፈጸሙ ዋና ዋና ጥሰቶች በሚል ሰባት ነጥቦችን ዘርዝሯል፡፡
በእነ ትፍስቱ አወሉን ቡድን በተመለከተ ደግሞ አምስት ነጥቦችን በመዘርዘር ሕግ ማክበራቸውን ይጠቅሳል፡፡
መግለጫው አንድነትን በተመለከተ በመጨረሻ እንዲህ ብሏል፡- ‹‹የእነ አቶ በላይ ፈቃዱ ቡድን ያካሄዱት የአመራር ምርጫ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና ከምርጫ ሕጉ ድንጋጌዎች ውጪ በመሆኑ ዕውቅና እንደማይሰጠው፤ በሌላ በኩል በእነ ትዕግሥቱ አወል ቡድን በቀን ጥር 16 ቀን 2007 ዓ›ም የተደረገው ጠቅላላ ጉባኤ በቡርዱ ዕውቅና ተሰጥቶታል፡፡ በመሆኑም ቦርዱ የእነ አቶ ትዕግሥቱ ዓወሉ ሁድን ፓርቲውን በመምራት ወደምርጫው እንዲገቡ በዛሬው ዕለት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ወስኗል››
መኢአድን አስመልክቶ መግለጫው አሁን ተመርጠናል በሚሉት በእነ አቶ ማሙሸት አማረ ሁድን የተፈጸሙ የህግ ጥሰቶች በሚል አራት ነጥቦች ዘርዝሯል፡፡ በሌላ በኩል በእነ አቶ አበባው መሐሪ ቡድን በኩል ያለውን እንቅስቃሴ የፓርቲውን ደንብ ያከበረ መሆኑን ጠቅሶ ‹‹የእሳቸው የምርጫ ሂደትም ሆነ የተመረጡበት የጠቅላላ ጉባኤ ውጤት ሪፖርት በቦርዱ ዕውቅና ተሰጥቶታል›› ይላል፡፡
መግለጫው በማጠቃለያው፣ አንድነትን እነአቶ ትዕግሥቱ አወሉ እና መኢአድን ደግሞ እነአቶ አበባው መሐሪ ፓርቲውን በመምራት ወደምርጫው እንዲገቡ በአንድ ድምጽ መወሰኑን ይገልጻል፡፡
መግለጫውን ያነበቡት አቶ ነጋ ዱሬሳ ወደመጨረሻ ላይ በፊታቸው ላይ ፍርሃት አዘል ስሜት በግልጽ ይነብባቸው ነበር፡፡ ከመግለጫው ከኋላ በቦታው የተገኘን ከ10 በላይ ጋዜጠኞች በርካታ ጥያቄዎችን ለመጠየቅ ብንነሳም ፕሮፌሰር መርጋ ‹‹ጥያቄ አትጠይቁን›› በማለት የቪ.ኦ.ኤ የአዲስ አበባ ዘጋቢ ጋዜጠኛ መለስካቸው አምሐ አንድ ጥያቄ በትግል ካቀረበላቸው በኋላ አጭር መልስ ሰጥተው ወዲያው ተነስተው ከአዳራሹ ወጥተዋል፡፡
መግለጫው እስር በእርስ የሚጋጩ ሀሳቦችን መያዙን የዚህ ዜና ዘጋቢ ለመረዳት ችሏል፡፡ ይህንንና ሌሎች ጥያቄዎችን ለመጠየቅ ብናስብም እነፕሮፌሰር መርጋ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ምክንያት ጥያቄ ለማቅረብ ዕድል ማግኘት ሳንችል ቀርቷል፡፡
በስፍራው የነበሩ የግል ጋዜጠኞች ‹‹ዘንድሮ ምን አይነት ምርጫ ልናይ ነው?›› በማለት በሀዘኔታ ሲናገሩ ተስተውሏል፡፡
source,-http://ecadforum.com/
Wednesday, 28 January 2015
በኢትዮጵያ መንግስት በጥብቅ የሚፈለጉ 3 አርቲስቶች
ከሮቤል ሔኖክ
እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ ሃሳብን በነፃነት ያለመግለጽ መብት አለመከበሩ ያጠቃው ጋዜጠኞችን ብቻ አይደለም። አርቲስቶችም ጋዜጠኞች ከሚከፍሉት መስዋእትነት ያልተናነሰ ትግል እያደረጉ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳለመታደል ሆኖ የሃሳብን የመግለጽ ነጻነት በመገደቡ ዛሬ እንደ ታላቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙና ተመስገን ደሳለን ያሉ ጋዜጠኞች ያልሆነ ክስ ተልጠፎባቸው በእስር ላይ ይገኛሉ። የእነዚ ታላላቅ ጋዜጠኞች ‘ወንጀል’ መንግስት እንደሚለው ሳይሆን የሕዝብን በደልና ብሶት ማሰማታቸው ብቻ ነው።
ዛሬ ዛሬ ደግሞ ላለፉት 23 ዓመታት ሃሳባቸውን በነጻነት ከሚገልጹት ጋዜጠኞች ባልተናነሰ በመንግስት ጥርስ እየተነከሰባቸው የሚገኙት የጥበብ ባለሙያዎች እየሆኑ ነው።
እንደሚታወቀው በስደት ዓለም ከ150 በላይ ጋዜጠኞች እንዳሉ ሁሉ ዛሬ ቁጥራቸው በዛ ያሉ አርቲስቶችም በስደት ይህንን ስርዓት በመሸሽ በስደት ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ መካከልም የኢትዮጵያ መንግስት እንደታላቁ እስክንድር ነጋ አስሮ ለማሰቃየት ከሚፈልጋቸው ታላላቅ አርቲስቶች መካከል 3ቱ ዋነኞቹ ሲሆኑ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ ገና መንግስት እያጎበጎበባቸው በመሆኑ የ3ቱን ገድል አሳይቻችሁ የሁለቱን እንስት አርቲስቶችን ማንነት አስተዋውቃችኋለሁ።
............1ኛ. ታማኝ በየነ
ብዙዎች እንደስሙ ነው ይሉታል። አክቲቪስት ሆኗል ከአርቲስትነቱ በተጨማሪ። አላሙዲ ካደረገለት በላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያደረገልኝ ይበልጣል በሚል ዛሬም ድረስ የያዘውን አቋም ባለማዋዠቅ ይህን ተራ መንግስት ማንነቱን በማጋለጥ ላይ ይገኛል። በብዙ ኢትዮጵያውያን ዘንድ “የሕዝብ ልጅ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ታማኝ በየነ አሁን በስልጣን ላይ ያለው አንባገነን ስርዓት ከዚህ አርቲስት ጎን ፎቶ የተነሳ፣ የታየ፣ ሻይ የጠጣ አሸባሪ ነው የሚል ክስ እንደሚመሰርት አስታውቋል። ታማኝ በየነ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ክብርን ያገኘ በመሆኑና ክብሩንም ለገንዘብም ይሁን ለታይታ ያልቀየረ በመሆኑ ብዙዎች የሚያከብሩት ሲሆን የሕወሓት መንግስት ይህን ታላቅ አርቲስት በቁጥጥሩ ስር ለማዋል የማፈነቅለው ድንጋይ የለም።
ታማኝ የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ሳይሆን በግሉ በሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ግፍ በነፃነት እያጋለጠ ዘረኛውን ስርዓት እርቃኑን እያስቀረው ሲሆን በተለይም መንግስትን የሚያጋልጠው ራሳቸው የመንግስት ባለስልጣናት በሚሰጡት እርስ በእርሱ በሚጣረስ በቪድዮ የታጀበ ቃለምልል መሆኑ በብዙሃን ዘንድ ተወዳጅነትን በሥርዓቱ ዘንድ ደግሞ ለመታሰር ከሚፈለጉ 3ቱ አርቲስቶች መካከል አንዱ ሆኗል።
.................2ኛ. ፋሲል ደመወዝ
አርቲስት ፋሲል ደመወዝን የማውቀው አዲስ አበባ ስድስት ኪሎ የሚባል ሰፈር በተለምዶው ሸለቆ የሚባል አካባቢ ነው። በሸለቆ አካባቢ ሲራመዱ ፋሲል ሙዚቃ በመለማመድ ላይ እያለ የሚያሰማውን እንጉርጉሮ ማድመጥ የተለመደ ነው። ይህ ታላቅ ድምፃዊ የጎንደር መሬት ለሱዳን ተላልፎ በሕወሃት/ኢሕአዴግ መንግስት በተሰጠበት ወቅት “አረሱት” የሚል ዘፈን ካወጣ በኋላ በስር ዓቱ ሰዎች ወፌ ላላ ተገርፏል። ፋሲል ታዝሎ እስኪሄድ ድረስ በዚህ ፋሽስት መንግስት የተገረፈ ከመሆኑም በላይ የዳነው በህክምና ብቻ ሳይሆን በጸበልም ጭምር ነው።
ፋሲል ደመወዝ አሁን ሰሜን አሜሪካ ከመጣ በኋላ ‘እንቆልሽ” በሚለው አልበሙ ‘ያውላችሁ’ የሚል ዘፈን ያወጣ ሲሆን በዚህም ዘፈኑ ሃገሪቱን ካለምንም ተቀናቃኝ በአፓርታይድ ስርዓት ለሚመሩት ሰዎች “ሰው አስተዳደራችሁን እና በደላችሁን ጥሎ ጥሏችሁ እየሄደ ነው” ሲል ነግሯቸዋል። ፋሲል ደሞዝ በአሁኑ ሰዓት በሕወሓት አስተዳደር ከሚፈለጉ ዋና አርቲስቶች መካከል አንዱ ነው።
....................3ኛ. ክበበው ገዳ
ኮሜዲያን ነው። በጣም ይወደዳል። በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያም ይቀልዳል – ክበበው ገዳ። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ እሱን የሚያል ኮሜዲያን አለ ብሎ ለመናገርም ይከብዳል ይላሉ በሙያው ውስጥ ያሉ ሰዎች እና ባለሙያዎች። ክበበው ገዳ በማንኛውም ማህበራዊ ሕይወት ዙሪያ በመቀልድ ይታውቃል። ይህ ኮሜዲያን ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ በመመላለስ የተለያዩ የኮሜዲ ሥራዎችን አቅርቦ ተመልሷል። የዘንድሮው ግን ለጉድ ነው። የሥርዓቱን ሰዎች በእጅጉ እስቆትቷል።
ባለፈው ኦገስት 2014 ላይ ክበበው ገዳ በዳላስ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ በዓል አስተናጋጅነት ትልቅ በዓል ላይ ተገኝቶ ነበር። ይህ ኮሜዲያን አሁን ባለው የኢትዮጵያውያን ነባራዊ ሁኔታ ዙሪያ በርካታ ቀልዶችን አቀረበ። በተለይም አሁን ባለው ስርዓት ዙሪያ ልክ እዚህ ሰሜን አሜሪካ ኮሜዲያን በመሪዎቻቸው እንደሚቀልዱት ሁሉ ቀለደ። የሕዝቡን ብሶትም በቀልዱ አሰማ። ስለሟቹ ጠ/ሚ/ር፣ ስለሟቹ ፓትሪያሪክ፣ አሁን ስላለው የመንግስት አካሄድ በቀልድ አዋዝቶ አቀረበ። ለዚህ ኮሜዲያን ከሕዝብ የቀረበለት አድናቆትን ቢሆንም ከ ስርዓቱ ግን የቀረበለት ማስፈራሪያና ዛቻ ነው። እንደውም ‘ሃገርህ ትገባታለህ” የሚሉ ዛቻዎች ከስርዓቱ ደርሶታል። ክበበው ሙያውን ተጠቅሞ ባስተላለፈው መልዕክት ከኢትዮጵያ መንግስት ተላላኪዎች የሚደርስበት ማስፈራሪያ ሃገርህ ብትገባ አለቀልህ የሚል ብቻ ሳይሆን አሁን ባለበት ሃገር ሳይቀር እንደማይለቁት የሚገልጹ ናቸው።
...............ማነህ ባለሳምንት?
ሜሮን ጌትነትና አስቴር በዳኔ።
ሁለቱም ሴት አርቲስቶች ናቸው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደርሰውን የሴት ልጅ ተጽ ዕኖ ተቋቁመው አደባባይ የወጡ ሴቶች። ሁለቱም ያመኑመትን ይናገራሉ። ሁለቱም በተለይ ሃገር ቤት ካሉ አርርቲስቶች የሚለዩበት ነገር አላቸው። እነዚህ አርቲስቶች ስለ እውነት እውነትን ስለመሰከሩ ዛሬ በ ሥ ር ዓቱ ሰዎች እየተነከሰባቸው ያለውን ነገር አብረን እያየነው ነው።
source.-http://www.zehabesha.com/amharic/?p=38449
Monday, 26 January 2015
የዕንቁ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር በእስር ላይ ይገኛል
የዕንቁ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆነው አቶ ፍቃዱ ማህተመወርቅ፤ የሃገር ውስጥ ገቢ መ/ቤት ‹‹ተገቢውን ግብር ለመንግሥት ገቢ አላደረክም›› በሚል ክስ ከጥር 13 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንዲውል አድርጎታል።
. አቶ ፍቃዱ ማህተመወርቅ
የዕንቁ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር በእስር ላይ ይገኛል
አቶ ፈቃዱ ከኢትዮጵያ ሆቴል በስተጀርባ በሚገኘው የቀድሞ ጉምሩክ መ/ቤት ወይም በአሁኑ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል መከላከል ዘርፍ የፀጥታና የሕግ ማስከበር ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት ቅጽር ግቢ በሚገኘው እስር ቤት የሚገኝ ሲሆን ፖሊስ ሐሙስ ጥር 14 2007 ዓ.ም ከቀኑ በዘጠኝ ሰዓት ከሠላሳ አራዳ ጊዮርጊስ ፍ/ቤት ያቀረበው ቢሆንም የዋስትና መብቱ ሳይጠበቅ ለጥር 21 ቀን ከቀትር በኋላ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶት ወደ እስር ቤት ተመልሷል።
አቶ ፍቃዱን ያሳሰረው የሃገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰቢያ መ/ቤት ‹‹የዕንቁ መጽሔት እየታተመች በነበረችበት ጊዜ የመጽሔቷ አሳታሚና ባለቤት ለመንግሥት ገቢ ማድረግ የሚገባቸውን 600 ሺኅ ብር አስቀርተዋል›› የሚል ሲሆን ፍ/ቤት ቀርቦም ‹‹ግለሰቡን በሕግ የምጠይቅበትን ሠነድ አሰባስቤ ያልጨረስኩ በመሆኑ ለሰባት ቀናት በእስር ላይ ይቆዩልኝ…›› የሚል ጥያቄ አቅርቦ ለጊዜው በፍርድ ቤቱ በኩል ተቀባይነት አግኝቷል።
የዕንቁ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆነው አቶ ፈቃዱ ማህተመ ወርቅ ‹‹ፖሊስ የመሰረተብኝ ክስ እኔን የሚመለከት አይደለም ›› ያሉ ሲሆን፤ በሕግ የሚጠየቁበት ጉዳይ ካለም የዋስትና መብታቸውን ሊያስነፍግ እንደማይችል፣ ሕጉም በአግባቡ የሚተረጎም ከሆነ ከእስር ነጻ የመሆን ዕድል እንዳላቸው ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
- See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=4118#sthash.2CpcMnqj.dpuf
አርቲስት አስቴር በዳኔ ከዚያ ሁሉ መንጋ ተነጥላ። ‘እውነት ነጻ ያወጣችኋል!’
የደደቢት ጉዞ መዘዝ፤ ከሰራዊት ፍቅሬ እስከ ታገል ሰይፉ
በመጀመርያ ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ደጋፊና ተደጋፊ የኪነጥበብ ባለሙያዎችን በሙሉ ጠሯቸው። ሰበሰቧቸው። እንዲህም አሏቸው። “ወደ ደደቢት አብራችሁን ትሄዳላችሁ፤ እዛ እንደደረሳችሁም አመጣጣችንንና አካሄዳችንን በደንብ አድርጋችሁ ታጤናላችሁ። ከዚያ ስትመለሱ ሁሉንም ነገር ለህዝቡ ትናገራላችሁ።…”
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የሃገር መሪ ሆነው የሚሰሩት እኝህ ሰው መልዕክታቸውን በዚህ አላበቁም። አይናቸውን ፈጠጥ፤ ጉሮሯቸውንም ጠረግ-ጠረግ አደረጉና ንግግራቸውን ቀጠሉ “ስለረጅሙና መራራው ትግላችን፤ ከጅምራችን እስከ አያያዛችን የታዘባችሁትን ሁሉ ንገሩን። ጥሩውንም ይሁን መጥፎውን ነገር ሳትደብቁ ተናገሩ።…”
ድምጻዊው በዝማሬ፣ ጸሃፊው በድርሰት፣ ተዋንያኑ በተውኔት ስለ ህወሃት የአርባ አመት ጉዞ እንዲመሰክሩ የተሰጠች ትእዛዝ መሆንዋ ነው። አጭር፣ ግልጽ እና ቀጭን መልዕክት ነበረች።
የስርዓቱ ደጋፊ ሳይሆን ይልቁንም ተደጋፊ የሆኑት ሁሉ የዘመቻውን ጥሪ በደስታ ተቀበሉ። ወደ ደደቢትም አመሩ። የታዘቡትንም ነገር ሲናገሩ ሰማን።
ልብ እንበል! እነዚህ የጥበብ ሰዎች ናቸው። ጥበብ ደግሞ የሕዝብ አገልጋይ ናት። ጥበብ ለእውነት የምትቆም ዘብ ናት። ጥበብ አንድን ህብረተሰብ የመቅረጽ እና የመለወጥ ሃይል አላት።
በአለማችን የጥበብ ሰዎች ሚና ጎልቶ የሚታየው ተፈጥሮ ባደላቸው የጥበብ ስራ ብቻ ሳይሆን፤ እነዚህ ሰዎች በጥበብ ስራቸው ውስጥ ለህዝብ በሚያስተላልፉት እውነተኛ መልእክትም ጭምር ነው።
አርቲስቶች አክቲቪስቶች መሆን አለባቸው ብሎ መከራከር አይቻልም። ይህ የራሳቸው ምርጫ ነው። መሆን ካለባቸው ግን የህዝብን እንባ ማበስ ነው የሚገባቸው። ወቅቱን ጠብቆ እንደሚቀየር ድሪቶ መንግስት ሳይሆን ከህዝብ ጎን መቆም ያስከብራቸዋል።
ጥበብ ቆራጥነትን ትጠይቃለች። መስዋዕትነትን ልታስከፍልም ትችላለች። ፍሬዋ ግን ሁል ጊዜ ጣፋጭ ነው። እውቁ ቻይናዊ አርቲስት አይ ዌዊ እዚህ ላይ ይጠቀሳል። አሜሪካዊቷ ጁዲ ችካጎም እንዲሁ። ጃማይካዊው ቦብ ማርሌይ እና የናይጄርው ፌላ ኩቲ በአለማችን ላይ ለውጥ ያመጡ የጥበብ ጀግኖች ናቸው። የኛዋ አርቲስት አስቴር በዳኔም ለዚህ ዋቢ ነች። ማህበራዊ ድረ-ገጾች ይህንን አስረግጠውልናል።
aster“ህዝቡ አጎብዳጆች ይለናል።” አለች አርቲስት አስቴር በዳኔ ከዚያ ሁሉ መንጋ ተነጥላ። ‘እውነት ነጻ ያወጣችኋል!’ የሚለው ክርስቶሳዊ አባባል የተዋሃዳት ወጣት። እውነትን ተናግራ ራስዋን ነጻ አወጣች። እርግጥም የህሊና ነጻነትዋን ለማወጅ መድፈር ነበረባት። ማማጥም ነበረባት። አርቲስትዋ እንደጦር የፈራችው ከፊትዋ ተደርድረው የነበሩ ጉምቱ ባለግዜዎች አልነበሩም። ምክንያቱም ጉዳዩን ለነሱ አስቀድማ ተናግራ ነበርና። ይልቁንም ከአጠገብዋ የነበሩ የስራ ባልደረቦችዋ እና የሙያ አጋሮችዋ እንደጦር ያስፈራሉ። እንደ ይሁዳ አሳልፈው ሊሰጧትም ይችላሉ። ደደቢት ላይ ሲደርሱ ሁሉም በአንድ ማሰብ ጀመሩ። ደደቡ… አንድ ግዜ ተኑሮ ለሚሞትበት አለም ሁሉም ከራሱ ተጣላ። ሁሉም ከህሊናው ሸሸ። ሁሉም ለማደር አጎብዳጅ ሆነ። በመጨረሻም ሁሉም አስቴርን በአርባ ክንድ ራቁዋት። ግና እርሷ ጣርያ ስትነካ እነሱ ደግሞ ሲዘቅጡ አየን።
የኪነ-ጥበብ ሰዎቻችንን መፈተኛ ግዜ ብቅ አለ። ግን ይህ ሁሉ ወጪ እና ሽርጉድ ለምን አስፈለገ?
ጉዞውን ከመጪው ምርጫ ጋር የሚያያይዙ ወገኖች አሉ። ጉዞውን እንደምርጫ ዘመቻነት ለመጠቀም…። ይህ የዋህነት ይመስላል። ምክንያቱም ህወሃት አንድም ግዜ በምርጫ ዘመቻና ግልጽ በሆነ ውድድር ምርጫ አሸንፎ አያውቅም። ነብሳቸውን ይማርና አቶ መለስ ከነ ስዬ ቡድን ጋር በተለያዩ ግዜ ተናግረውታል። “ህወሃት በስብሷል!” ነበር ያሉት። ላለፉት ፪፫ አመታት ይህ የበሰበሰ ስርዓት ነው ሃገሪቱን እየገዛ ያለው። ይህ የበሰበሰ ስርዓት በምርጫ ሳይሆን የህዝብን ድምጽ በመስረቅ ነው እስካሁን ያለው።
ከምናከብራቸውና ከየምናደንቃቸው የኪነጥበብ ስዎች ውዳሴዎች ሰማን። ንዋይ ደበበም እጅግ አድርጎ ሲረግመው በነበረው ደደቢት ላይ ዘፈነ። እንዲያውም በስሜት ዘፈነ። “የሃገር ነቀርሳዎች” ሲላቸው የነበሩትን እነ ሳሞራን፣ እነ አባዱላን፣ … እያቀፈ … አልረሳም እያለ አቀነቀነ።neway serawit
በዚያ የቀውጢ ወቅት ከሰለሞን ተካልኝ ከተቃዋሚ ወገን ወጥቶ ህወሃትን ሲቀላቀል ድምጻዊው ነዋይ ደበበ እንደ እብድ ነበር ያደረገው። ያዙኝ፤ ልቀቁኝ አለ። የንዴት ቃላትን ሁሉ በዘፋኙ ላይ አዥጎደጎደው። “ማሰብ የማይችል ደደብ ሰው!” አለ ነዋይ። ቀጠለናም “ሰለሞን ተካልኝ ስጋ የሚበላ በሬ ነው።” ሲል ድምጻዊውን ከሰብአዊ ፍጡርነት ወደ እንስሣነት ጎራ መድቦት ነበር።
ዛሬ በዚያው መድረክ ላይ አዲስ ትእይንት እያየን ነው። የግዜ ሃዲድ ላይ ሆኖ የሚመለከተው ሁሉ በትዝብት የሚያስቆዝም አሳዛኝ ድራማ፤ አርቲስት ብለን የምንጠራቸው ወገኖቻችን የሚፈጽሙት የፖለቲካ ዝሙት። ነዋይ ደበበ በግዙፉ የሰለሞን ተካልኝን ትከሻው ላይ ለመጠምጠም እጆቹ በጣም ሲረዝሙ በመገናኛ ብዙሃን ተመለከትን። … አጃኢብ አለ ያገሬ ሰው!
አዕምሮ ማሰብ ሲያቆም፣ አንገታቸው አዙሮ ማየት ሲሳነው፣ ልቦናችን የቅርቡን ክስተት ሲዘነጋ፣ የስነ-ልቦና ችግር ነው ከማለት ውጭ ምን ይባላል?
የሰራዊት ፍቅሬ ማጎብደድ ደግሞ ተወዳዳሪ አልተገኘለትም። ይህ ሰው በ፩፱፹ዎቹ በነበረው የርስ በርስ ውግያ ወታደር ሆኖ ከደርግ ወገን ነበር የተሰለፈው። ዛሬ በሽሬ ሽንፈቱ ላይ ጥሎት የሸሸው የጦር ታንክ ላይ ቆሞ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እጆቹን እያወጣ ደግም ቀለደ። ለካስ ደርግ እንደዚህም አይነት ወታደር ይዞ ነበር ህወሃትን ይፋለም የነበረ? ሰራዊት ፍቅሬ ዛሬ ዝናው ሳይሆን ሃብቱ ጣርያ ነክቷል። አሰልቺ ድምጹና ምስሉ እጅ-እጅ እስኪል በቴሌቪዥን እንዲቀርብ በገዢው ፓርቲ ተፈቅዶለታል። ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ የሚውሉ የስርዓቱ በዓላት ቁጥር እጅግ በዝተዋል። የብሄር ብሄረሰቦች ቀን፣ የከተሞች ቀን፣ የአርሶ አደሮች ቀን፣ የአርብቶ አደሮች ቀን፣ … ባዛር ለልማት ወዘተ። የማስታወቂያ ወጪው ከዝግጅቱ ወጪ አይተናነስም። ሁሉንም የማስታወቂያ ስራ ለሰራዊት ፍቅሬ ሰጥተውታል። ታዲያ እሱም ገሚሱን ለባለስልጣናቱ ማካፈሉ የግድ ነው። የዚህ ሰው መንቀልቀል ምስጢር ይህ ብቻ ነው። ሰራዊት ፍቅሬ በዚህ ሁኔታ የማስታወቂያ ስራውን በሙስና መስመር ውስጥ አዝልቆታል።
አንደኛው ተደጋፊም ተነስቶ ”ይህ ነገር በአፍሪካ አንድነት ድርጅት ፊት ለፊት ሃውልት ሊሰራለት ይገባል።” ሲል ተደመጠ። ሰውዬው ይህንን አምኖበት እንዳልተናገረ ሰዎቹም ይገምታሉ። መቼም ለእለት ጉርስ ሲባል እንደዚህ አይነት ለህሊና የሚጎረብጥ ነገር እያደረጉ ከመኖር፤ በልመና መተዳደር ክብር ነው።
ከጅምሩ የስርዓቱን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ሂደት ለመገምገም ወደ ደደቢት በረሃ መሄድም አያስፈልግም። ኢትዮጵያ ዛሬ ከገባችበት መከራ ለማውጣት የህወሃት አነሳስን ማጥናት ምንም ፋይዳ የለውም። መነሻው ጥሩም ይሁን መጥፎ፣ መድረሻው ግን አላማረም። ይህ ስርዓት ሃገሪቱን ባህር አልባ አገር አድርጓታል። የባህር በር የአንድ ሃገር ምስጢርም ነው። ኢትዮጵያ እንደ ማንኛውም ሉአላዊ ሃገር ምስጢር እንኳን የላትም።
ህዝቧም ከአፈናው ሰንሰለት ገና አልወጣም።
በአመለካከት ልዩነታቸው ብቻ ወገኖቻችን እንደ ጥጃ ሲታሰሩ የደደቢት ተጓዦቹ ይመለከታሉ። ሃሳባቸውን በነጻ የገለጹ ዜጎች የሽብርተኛነት ታርጋ ተለጥፎላቸው በግፍ ሲፈረድባቸው ይሰማሉ። ኢትዮጵያውያን እንደ ምጽዓት ሲሰደዱ በአይናቸው ይመለከታሉ። ለነጻነትና ለእኩልነት ታግለን መጣን የሚሉን ደግሞ በአንዲት ጀንበር ሚሊየነር ሲሆኑ ይታዘባሉ። ይህ ሁሉ ሲሆን ታዲያ እንደሙያቸው አንዲት ቃል እንኳን ተንፍሰው አያውቁም። ወደ በረሃው መጓዙ እንደ ሲሲሊው የማፍያ ቡድን ከደደቢት ምሽግ ውስጥ ቃል-ኪዳን ለመግባባት ካልሆነ በቀር ፋይዳው አይታይም።
“ህዝቡ አጎብዳጆች ይለናል።” አለች አስቴር በዳኔ። ህዝብ ምን እንደሚላቸው የምትሰማው እርሷ ብቻ አይደለችም። ጆሮ ያለው ሁሉ ይሰማዋል። ይህን እያወቁ ግን አጎብዳጅ ምሆናቸውን ጭራሽ በብሄራዊ ቴሌቭዥን ወጥተው አሳዩን።
ህዝቡ ብቻ አይደለም። በእርግጠኝነት ለመናገር እነዚያ ባለ-ስልጣናትም አድርባዮቹን ይንቋቸዋል። በባህር ዳሩ የኢህአዴግ ጉባኤ “የኢህአዴግ አባል ለመሆን አንዱና ዋናው መስፈርት አድርባይነት ነው” በማለት አድርባይነትን የፈጠረውና ያስፋፋው ራሱ ህወሃት እንደሆነ ተናግረው ነበር። “አድርባይነት” ስርዓቱን በሚፈታተን ደረጃ መስፋፋቱን ከመግለጻቸውም በላይ አድርባዮቹን እንዴት እንደሚበቀሏቸውም ባህርዳር ላይ መክረዋል።
ደብረጽዮን ትእዛዙን ሲሰጡ ትንሽም ቢሆን ዲፕሎማት ነበሩ። ከትእዛዞቻቸው መሃል እንዲት እንዲህ የምትል መልእክት ነበረች። “…ችግሮቻችንንም ንገሩን።”
ይህች ሃረግ የኪነ-ጥበብ ሰዎቹ የህዝብን ብሶት በአደባባይ እንዲናገሩ በር ከፋች ነበረች። እነ አበበ ባልቻ ይህችን እድል ተጠቅመው ስለ-ኪነጥበብ መውደቅ እንኳን ትንሽ መልእክት ከማስተላለፍ ይልቅ ልወደድ ባይነትን መረጡ። ይህን ጥሬ ሃቅ የመናገር ድፍረት ያለው አንድ ሰው ጠፋ። ሁሉም ምስጋናና ውዳሴውን አበዛ። ለማደር የሚደረግ ካንገት በላይ ውዳሴ … መቼም ያሳዝናል።
በጭምጭምታም እንደሰማነው፤ በደደቢት አንዳች የተለወጠ ነገር የለም። ደደቢት ድሮም በረሃ – አሁንም በረሃ ነው። የአካባቢው ህዝብ ላይም ምንም የሚታይ ለውጥ የለም። ይህ ህዝብ ከሃያ አመታት በፊት የመናገር መብት አልነበረውም። ይህ መብት አሁን ብሶበት ሕዝቡ የመናገር ብቻ ሳይሆን የውጭ ራዲዮ እንኳን የመስማት መብቱን ተነፍጓል።
ይህችን ሃቅ የጎበኘ አንድ የኪነ-ጥበብ ባለሞያ እንዴት አስችሎት ዝም ይላል? ይህ የብዙዎች ጥያቄ ነበር። “ስለ እውነት የቆመ አንድ ሰው ይጥፋ?” የሚለው ጥያቄ በህዝብ ዘንድ እየተብላላ እያለ ነበር አስቴር በዳኔ ብቅ ያለችው። ይህች አርቲስት የህዝቡን ጥያቄ ይዛ በድፍረት ወረወረችው። መገናኛ ብዙሃንና ማህበራዊ ገጾችም በዚሁ ጉዳይ ተጨናንቀው ከረሙ።
ለድቅድቅ ጨለማ ትንሽ የብርሃን ፍንጣቂ ትበቃለች እንዲሉ የዚያን ሁሉ የውሸት ክምር አንድ እውነት አፈራረሰው። ህዝብ ያከብራቸው የነበሩ የኪነጥበብ ባለሞያዎች ሁሉ ወረዱ። የማያልፈውን የህዝብ ፍቅር በሚያልፍ ነገር ቀየሩት።
ጥሪ የተደረገላቸው አርቲስቶች ሁለት አማራጮች ነበራቸው። ጥሪውን ተቀብሎ ሄዶ እውነትን መመስከር አሊያም እንደ ገጣሚ ታገል ሰይፉ ጥሪውን አለመቀበል። ገጣሚ ታገል ሰይፉ በኤፍ ኤም ፱፯ ራዲዮ ሲናገር እንዲህ ነበር ያለው።
“ባለፈው የመቀሌ ጉዞ ላይ እኔ አልሄድኩም። አርቲስቶች ሲሄዱ ጥሪ ተደርጎልኛል። ነገር ግን የደደቢቱን ጉዞ ስላላመንኩበት ቀርቻለሁ። ስለማልፈልገው ማለት ነው። … ለነሱም የምለው ነው። በተለይ ባለፉት 15 አመታት ብዙ ነገር አልተሰራም። ለስነ ጽሁፍ የሚመች ግዜ አይደለም። ስነጽሁፍን ትኩረት አልሰጡትም። እያየን ነው።“
ታገል ሰይፉ ቀደም ሲልም በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሃሳቡን ተቆርጦ እንዳስቀረበት ተናግሯል። ደደቢት ድረስ ሄዶ ሃሳቡን የማያስተላልፉለት ከሆነ መቅረቱ አይነተኛ አማራጭ ነው። አበበ ባልቻን፤ ሙሉ አለምን፣ ነዋይ ደበበን፣ … አርቲስቶች እና የኪነጥበብ ሰዎች ብለን ጠርተን፤ አስቴርንና ታገል ሰይፉን ምን ልንላቸው ይሆን? … ማህበራዊ ፍርዱን ከህዝቡ ያገኙታል።
ህወሃት ግን አንድ መልዕክት ለማስተላለፍ ነበር አርቲስቶቹን ወደ ደደቢት የወሰዳቸው። እዚህ ተነስተን፣ አፈር ለብሰን፣ አፈር በልተን፣ የፈረስ ሽንት ጠጥተን የያዝናት ስልጣን ናት። ይህችን ስልጣን በምርጫ እንደማናስረክብ እናንተም አረጋግጡልን … እንዲሁ ተቃጥላችሁ ታልቃላችሁ እንጂ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ አታስቡ … የሚል መልዕክት።
እኔም በዚህች ቀልድ ጽሁፌን ልቋጭ። አንድ የህንድ ኢንቨስተር አዲስ አበባ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያንን የቀብር ስፍራ አይቶ በሊዝ ሊገዛ ፈለገ። የአዲስ አበባ ባለስልጣናትን ጠርቶ እንዲሸጡለት ጠየቀ። ባለስልጣናቱም መልሰው ሌሎች ቦታዎች ሳያልቁ የቀብር ስፍራ ለግዜው እንደማይሸጡለት ነገሩት። ህንዱ መለሰና መከራቸው። “እኛ አገር ሰው ሲሞት እናቃጥላለን እንጂ አንቀብርም። ለምን ይህን ለም ቦታ ታባክናላችሁ?” ባለስልጣናቱ መለሱ፣ “እኛ አገር ደግሞ ሰውን በቁሙ ነው እንጂ ሲሞት አናቃጥልም!”
SOURCE,-http://www.goolgule.com/trip-to-dedebit-serawit-to-tagel/
የደም አኬልዳማ
ወያኔ ዛሬም መግደል ማሰርን ህዝብን ማሰቃየቱን ቀጥሏል ጩቁኑ ህዝብ በወያኔ ቅልብተኞች ድብደባ እየተፈፀመበት ነው ።ወዴት ነው ጉዞው ፍታዊ እና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ በእውነት በኢትዮጲያ አለ? ዲሞክራሲን ህዝብ ከሻታ ቆየ ወያኔ ግን ህዝቡን እንደ አህያ መርገጡን አላቆመም።ቀን አንድነት የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ከባድ የሆነ እርምጃ ወስዷል ምርጫ ከማን ጋር ነው ፉክክሩ? ወያኔ እራሱ ብቻውን ተወዳድሮ ብቻውን ለማሸነፍ ይመስል ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ማሰር እና ማሰቃየቱን ቀጥሏል ።አንዱ ለአንዱ መተማመን ቀርቷል እንደ አሸን በፈሉ ጆሮ ጠቢዎች (ደህንነቶች) ሃሳብን በነፃነት ለመግለፅ እንኳ አልተቻለም ።
ምርጫ ተባለ ማነው የሚወዳደረው ሁሉም በእስር ናቸው ።ዲሞክራሲን ምርጫ መናፈቅ ማለት በሬን ውለድ እንደማለት ነው ወያኔ ህዝብን እያሰቃየ መግዛት እንጂ በዲሞክራሲ ምርጫ ይወርዳል ብሎ ማሰብ የዛሬን የቀን, , ,የአንድነትን ሰልፍ በቀላሉ እንደምሳሌ ማንሳት ይቻላል።
bostd by samuel adem
Friday, 23 January 2015
“ለልጆቼ የማይሆን ተስፋ አልነግራቸውም” የነፃነቱ ታጋይ አንዳርጋቸው ፅጌ
ከልጅ አያሌው
ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ትግል እስከወዲያኛው ከዳር ለማድረስ ቆርጦ ልጆቼን ቤተሰቦቼን ሳይል ከራሱ በላይ በሀገሩ ፍቅር ተበልጦ የተሻለ ነው የሚለውን፣ አማራጭ የሌለውን፣ የኤርትራን ጫካ መርጦ የማይቻል የሚመስለውን ችሎ ብዙዎች ፈቀቅ ማድረግ ያቃታቸውን የመተባበር የመያያዝ በአንድ ገብቶ ለአንድ አላማ የመታገልና ኢትዮጵያን እንደቀደመው ታላቅ ሀገር የማድረግ ውጥን የተሻለና የሚያግባባ ሀሳብ በመሸከፍ ከሚመራው ንቅናቄ ከግንቦት 7 ጋር እጅግ እውነት የማይመስሉ ድንቅ ስራዋችን በመስራት ጠማማውን በማቅናት ኮረብታውን በመደልደል አንድ መሆን ሳይችሉ ለአመታት ሲኳትኑ የነበሩትን በኢትዮጵያዊነት እንዲተሳሰሩ በማድረግ ፍቅር የሰራ ትልቁን መሰረት የጣለ ምርጥ የኢትዮጵ የቁርጥ ልጅ አንዳርጋቸው ፅጌ።
ዛሬ እሱ በማረፍያው ሰዓት አግባብ ባልሆነ መንገድ ከአውሬዋች እጅ ወድቆ ይህን መልዕክት አስተላልፏል። ለልጆቼ የማይሆን ተስፋ አልነግራቸውም።
ይሄ መልዕክት ኢትዮጵያን ለሚወዱ ሁሉ እጅግ የሚያም ነው ምክንያቱም እየከፈለ ያለው መሰዋት ለኛ ለኢትዮጵያኖች ስለሆነ።
አንዳርጋቸውን ከግንቦት 7፣ ግንቦት 7ን ከአንዳርጋቸው መነጠሉ የማይሞከር ነው ምክንያቱም ሀቁ የሚነግረን እሱና እሱን ከሚመስሉ ወንድሞች ጋር ታላቅ የሆነ ኢትዮጵያን የማዳን ራዕይ ሰንቀው በግድ ሳይሆን በፍቅር ተሳስረው አንዳይነት አላማ አንግበው ማድረግ ከሚችሉት በላይ ሌተቀን ደከመን ሰለቸን ሳይሉ ከማንም በላይ የየግል ህይወታቸውን መኖር እየቻሉ ያለመታከት ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ታላቅ ለማድረግ የተሰለፉለት አላማ መሆኑ በግልፅ የሚታይ ሀቅ ስለሆነ።
ታድያ አንዳንዶች የኢትዮጵያዊነትን ካባ የለበሱ የሚመስሉ እየደረሰበት ያለውን ስቃይ በመኮነን ድንቅ ሰው ታላቅ ሰው መሆኑን አክለውበት ጀግናችን ነው ብለው ሲያበቁ አንዳርጋቸውና ንቅናቄው አምነውበት: በአሁን ሰአት ካለው የሀገራችን አንዲሁም የጎረቤት ሀገራት ሁኔታን በማጤን አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን በመረዳት በትግል የዘረጉትን ገመድ በጥሶ ለመጣል ያስችለናል የሚሉትን የሰነፍ ስንቅ በመሰነቅ እየተሄደበት ያለውን መልካም መንገድ ፈንጂ የተጠመደበት በማስመሰል አንዳንዴ በዛበኩል ትግል ለሚያደርጉት ከልብ ያዘኑ በመምሰል አልሆን ሲላቸው ደግሞ በዛ በኩል የሚደረግ ጉዞ ለሀገር አደጋ አለው በማለት ነጋ ጠባ ያለ ህፍረት መከራቸውን ሲያዩ ስምለከት ከሚቆረጥላቸው አበል ጥቂቱን እንኳን ደጉሜ ነፃ ሰው ባደርጋቸው እልና ፀረ ትግልና ፀረ ነፃነት መሆናቸው ሲታወሰኝ ከእንዲህ አይነቱ ሱስና አመል ማላቀቁ ከአቅሜ በላይ መሆኑን ሳውቀው አንድላይ ደባልቆ ማሸቱን እመርጥና እተወዋለው።
በነገራችን ላይ ይሄ አባዜ በነዚህ እኩይ ተግባር ባላቸው ጥቂት ሰዋች ብቻም አይቀነቀንም ይልቁንም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊነት ያለምንም ማወላወል አንገታቸውን ሊሰጡ በሚችሉ ሰዋችም ወቅት አየጠበቀ እንደሚያጓራ ዛር ሲያወራጫቸው ይስተውላል ታድያ የችግሩን መንስኤ ሳጠናው ፍቅር ሆኖ አግኝቸዋለው ፍቅር ደሞ እዚ ውስጥ ምን ከተተው ትሉኝ ይሆናል? ይሄኛው ወዲህ ነው አትጣበቅ እንጂ አንዴ ከተጣበክ አትታጠር እንጂ አንዴ አጥር ከሰራህ ማየትም መስማትም የምትፈልገው ያፈቀርከውን ብቻ ነው ወገኖቼ በድርጅት ፍቅር እንዳታብዱ የትም ስለማያደርስ :አንዴ ግን ከተለከፋቹ የተሰራው እናንተ ካልሰራችሁት የተጀመረው እናንተ ካልጀመራችሁት የታሰበው መልካም ሀሳብ ከናንተ ቀድሞ ካልፈለቀ ገደል አፋፍ ላይ ነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ተይዛቹ እንኳን የማዳን እጅ ቢዘረጋ አይናቹ ማየት የለመደውና የምታፈቅሩት እጅ አለመሆኑን ስታውቁ መዳንን ትፀየፉታላቹ ገደል መግባቱን ትመርጣላቹ ስለዚ እውነት ሀገራችንን ማዳን ከፈለግን ሜዳው ሰፊ ነውና እኔ ካልባረኩት የሚለውን ፍሬ ከርስኪ ትተን ሌላውን ከመጎተት የተሻለ የምንለውን ሜዳ በመምረጥ ለሀገራችን አለኝታ እንሁን።
ሌላኛው ደግሞ እጅና እግሩ ተጠፍንጎ የታሰረበት ይመስል ከማሳየት ይልቅ ጥግ ይዞ የታላቹ፣ የት ገባቹ፣ ጦርነት የሆሊውድን ፊልም አይነት እየመሰው በከንቱ ምኞት መሬት ላይ ወርዶ ህይወቱን ለሀገሩ አሳልፎ ለመስጠት ነጋ ጠባ መከራውን የሚያየውን የነፃነቱን አርበኛ ከሶፋው ላይ ተደላድሎ ተቀምጦ እግሩን ጠረጴዛ ላይ ሰቅሎ ቢራውን እየተጎነጨ ከኮንፒውተር ጀርባ ሆኖ ሲከተክተው ይውላል ደሞ እፍረትም የለውም ትግላችን፣ የኛ ትግል፣ እያለ እየደጋገመ ሲናገር ይደመጣል እኔ ግን እላለው: መጀመርያ እጃችንን ከኪሳችን ታግለን ነፃ እናውጣው። ሀገራችንን ለማዳን የሚደረገውን ትግል ለመደገፍ ሰበብ አንደርድር።
በመጨረሻም አንድ ወዳጄ ለጨዋታ ባወረዳት ቅኔ ለጠቅ አድርጌም የኔንም የመልስ ምት አክዬ ልደምድም፣
እኔ እናገራለሁ ቆሜ ከፊታቹ
ጠሀይ አልወጣ አለች ከሰሜን ወርዳቹ
መልስ
የጠሀይን መውጫ ልብህ እያወቀው
ብላ ተኛ ሆነህ የቆረጠውን ሰው
በየትኛው ወኔነው የምትጠይቀው
ቅኔው የወዳጄ ሆና እሱ ባያቀነቅናትም ይህቺን ዘፈን ብዙዋች ይዘፍኗታል እስኪ ካስተማረች በተን ላድርጋት፣
ለመሆኑ የጠሀይ መውጫ በሰሜን ሆነ እንዴ? የኔ ጥያቄ ነው ጠሀይ በምስራቅ ወጥታ በምዕራብ ትጠልቃለች የወዳጄ ጠሀይ ግን :ከወትሮው ለየት አለችብኘ ለነገሩ ራቅ አድርገው ካሰቡት ጠሀይ በእድሜም የጠገበች እንደመሆኗ ተወዳጅነቷ ዋዛ እንደማይሆን አልጠራጠርም።
ወዳጄም የመናፈቅ ብዛት ሳያናግረው አልቀረም ስለዚህ ወንድሜ ጠሀይን እኛ አላገድናትም መውጫዋም በምስራቅ ነው እኛ ግን መንደርደርያ የለንምና በሰሜን ከተናል ባይሆን ባገኘናት እድል ተጠቅመን ከሰሜን ተነስተን የጠፋችብህን ጠሀይ ከዚህ ሰፈር ሳይሆን ሰፈሯ ድረስ በመምጣት ብቅ እንድትል ማረጋችን እንደማይቀር ላረጋግጥልህ እወዳለሁ የምትቸኩል ትዕግስት የሌለህ ከሆነ ግን ጠሀይ ብቅ እንድትል ስትፈልግ በደቡብ፣ ስትፈልግ በምዕራብ፣ የሚያስጠጋህ ከገኘህ በዛ በኩል ሞክር።
ምስራቁ ቅርብ ነውና ባትደላደል እንኳን ጫፍ የሚያስይዝህ ካገኘህ ያው መደወል አትወድም ምልክት አድርግልኝ ያለህበት ድረስ መጥቼ እቀላቀልሀለው እውነቴነው የምልህ ጠሀይቱ እናቴ ጋር እስካደረሰኘ ድረስ የማልቆፍረው ገድጓድ የማልወጣበት ተራራ፣ የማልሞክረው አቋራጭ አይኖርም።
በሰሜን የከተቱት ብዙ ጊዜ ተጠይቀው ሲመልሱት ካደመጥኩት ቅንጭብ የተወሰደ ነው በሚል ይያዝልኝ።
ስለዚ መጠላለፉን ትተን የምንችለውን እናድርግ ያ ከሆነ ትግሉን መሬት ላይ አውርዶ እየሰራ ያለውም በአየር ላይ ያለውም በመጨረሻዋ ቀን የነፃነቷ ጠሀይ በሀገራችን ስትወጣ እኩል ይቋደሳሉና።
ይህንን ለመፃፍ ያነሳሳኝ “ለልጆቼ የማይሆን ተስፋ አልነግራቸውም” የሚለው የጀግናው ታጋይ የአንዳርጋቸው ንግግር መሆኑነ አሰምርበታለሁ።
በዘገየን መጠን የምናጣው ይበዛልና ባለመጠላለፍ ወደፊት እንሂድ፣ እኔ የሁሉም ነኝ የተሻለ አማራጭ ያለው ይገዛኛል።
ኢትዮጵያ ለዘላላም በክብር ትኑር!
እናቸንፋለን!
ልጅ አያሌው
source,-http://www.zehabesha.com/amharic/?p=38237
Thursday, 22 January 2015
አሳዛኝ ዜና ሳሪስ ቻይናዊ 3 ተማሪዎች ሕይወት ቀጠፈ
አሳዛኝ ዜና ሳሪስ የባቡር ፕሮጀክት ስራ የሚሰራ ቻይናዊ በሎደር ማሽን የፍሬ ሕይወት ት/ቤት አጥር በመደርመስ 3 ተማሪዎች ሕይወት ቀጠፈ
ዛሬ ጥር 14 ቀን 2007 ዓ.ም ከቀኑ 5፡30 ሳሪስ ካዲስኮ የባቡር ፕሮጀክት ስራ የሚሰራ ቻይናዊ በሎደር ማሽን የፍሬ ሕይወት ት/ቤት አጥር በመደርመስ በስፖርት ክፍለ ጊዜ ግቢ ውስጥ የነበሩ 3 ተማሪዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ በርካታ ተማሪዎች ከፍተኛና መካከለኛ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሕክምና ቦታ ሄደዋል፡፡
በተጨማሪም በቅርብ እርቀት ቡና ቦርድ እየተባለ በሚጠራው ግቢ ውስጥ ቻይናው የጥበቃ ሰራተኛውን ሲመታው ለመከላከል ሲል በያዘው አጣና ሲመታው በአካባቢው የነበሩ ፖሊሶች ሁለቱንም ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸዋል፡፡
የሕፃናት ተማሪዎች ያለአግባብ መሞት የፍሬ ሕይወት ተማሪዎች በአስነሱት ከፍተኛ ቁጣ የአዲስ አበባና የፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ ድብደባ በተማሪዎች ላይ አድርሷል፡፡ እጅግ በጣም የሚያሳዝነው የሕፃናቶች ሞት ሳይታሰብ ቻይናውያንን የፌዴራል ፖሊስ በማጀብ በተዘጋጀላቸው መኪና ወደ ቤታቸው ሲሄዱ የህዝብ መገልገያ በሚመስል ታክሲ በርካታ ተማሪዎች ወደ እስር ቤት ተጉዘዋል፡፡ በአካባቢው ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል፡፡
.
source.-http://satenaw.com/amharic/archives/3902
የህወሓት ኣባል ኣልሆንም ያለ ኣስተማሪ በባለ ስልጣናት ከፍተኛ ድብደባ ደረሰበት
ፎቶው የምታዩት ሰውየ ገብረየሱስ ገብረሂወት የተባለ ኣስተማሪ ነው።
የምታዩት ፎቶ የህወሓት ኣባል ኣልሆንም ያለና በባለ ስልጣናት ከፍተኛ ድብደባ ደረሰበት ኣስተማሪ ነው።
መምህር ገብረየሱስ ገብረሂወት በደጉዓ ተምቤን ማሕበረስላሴ ትምህርት ቤት የሚያስተምር ነው።
የድብደባው መነሻ የህወሓት ኣባል ሆኖ መቀጠል ኣልፈልግም በማለቱ የመጣበት ጦስ ነው። ጦሱ ከደምወዙ በቀጥታ ለህወሓት ኣባልነት የሚል በየወሩ ሲቆረጥ ፍቃደኛ ባለ መሆኑና በተደጋጋሚ ሲቆረጥበት ወደ ፍርድ ቤት ሂዶ በመክሰስ ያለፍላጎቱ እንዳይቆረጥበት የሚል ፍርድ በመሰጠቱ የተበሳጩ የወረዳው ሃላፊዎች የወሰዱት ኣብዮታዊ እርምጃ ነው። ነፃ እርምጃ ማለት እንዲህ ኣይደለም..?
ህዝቡ ሳይወድ በግድ ኣባል ሁን ተብሎ የሚቆም መንግስት ምንያህል ዘለቄታ ይነሮዋል..? የደጉዓ ተምቤን የህወሓት ሃላፊዎች ግፋችሁ ለከት ብታበጁለት ይበጃቹሃል እንላለን። ገብረየሱስ ገብረሂወት ድብደባ ከደረሰበት በሗላ በከተማው ተጥሎ እስከ ለሊት ኣስር ሰዓት ተጥሎ ኣምሽተዋል።
ነፃነታችን በእጃችን ነው…!
..........IT IS SO…! Amdom Gebreslasie
- See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/3872#sthash.dFj1sFOX.RzQ0UBR2.dpuf
“ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም” በኢትዮጵያ የመገናኛ-ብዙሃን ነጻነት ላይ የሚፈፀም የመብት ጥሰት
(Human Rights Watch) የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) እ.ኤ.አ. በ2010 ዓ.ም. በተካሄደው ምርጫ 99.6
በመቶ የፓርላማ መቀመጫን ካሸነፈ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት ሃሳብን የመግለጽ ነጻነትን እና መረጃ
የማግኘት መብትን በመገደብ በግል መገናኛ-ብዙሃን ላይ እያሳደረ ያለውን አሉታዊ ተጽዕኖ አባብሶታል፡፡ እ.ኤ.አ.
ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ ቢያንስ 60 ጋዜጠኞች ሃገር ለቀው የተሰደዱ ሲሆን ሌሎች 19 ጋዜጠኞች ደግሞ በእስር ላይ
እየተሰቃዩ ይገኛሉ፡፡ መንግስት በደርዘኖች የሚቆጠሩ ህትመቶችን ዘግቷል፤ እንዲሁም አብዛኛዎቹን የቴሌቪዥን
እና የሬድዮ ስርጭቶች በቁጥጥሩ ስር በማድረግ ኢትዮጵየዊያን የሀገር ውስጥ የፖለቲካ ጉዳዮችን በተመለከተ ነጻ
መረጃ እና ትንታኔ የሚያገኙበትን እድል አጣቧል። በግንቦት 2007 በሚካሄደው ምርጫ መገናኛ-ብዙሃኑ ህዝቡን
በወሳኝ ጉዳዮች ላይ በማስተማርም ሆነ መረጃ በመስጠት ረገድ ቁልፍ ሚና ሊጫወቱ ይችሉ ነበር፤ እንዲሁም
የመከራከሪያ መድረክ በመሆን ሊያገለግሉ ይችሉ ነበር፤ ይሁን እንጂ መንግስት በሃገሪቱ ላለው ብቸኛ የበላይነት
የግሉን መገናኛ-ብዙሃን እንደ ስጋት አድርጎ በመውሰድ የግሉን መገናኛ-ብዙሃን፣ ነጻ ጋዜተኝነትን እና ተቺ ትንታኔን
ለማጥፋት የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ላይ የሚገኝ ሲሆን ይህም የከፋ ውጤት አስከትሏል።
የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ የሆነው የኮሚቴ ቱ ፕሮቴክት ጆርናሊስትስ (Committee to protect Journalists)
መረጃ እና የሂዩማን ራይትስ ዎች ጥናት እንደሚያመለክተው ኢትዮጵያ ከኢራን በመቀጠል በዓለም ላይ በርካታ
ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞችን ለስደት የምትዳርግ ሀገር ሆናለች። የመንግስት አካላት አፋኝ ህጎችን መሰረት አድርገው
ጋዜጠኞች በየወቅቱ ያሉ ክስተቶችን እና ጉዳዮችን አስመልከተው በሚሰሩት ዘገባ እና ትንታኔ ምክንያት
በተደጋጋሚ ክስ ይመሰርቱባቸዋል፤ ፍርድ ቤቶችም ክሱን ተከትለው የጥፋተኝነት ውሳኔ ያስተላልፋሉ፡፡ በአሁኑ
ወቅት እስክንድር ነጋን እና ርዕዮት ዓለሙን የመሰሉ ግለሰቦች በአዲስ አበባ እና በክልሎች የሚገኙ ተለይተው
የሚታወቁም ሆነ የማይታወቁ ከደርዘን በላይ የሚሆኑ ጋዜጠኞች እየደረሰባቸው የሚገኘውን ፈተና የሚያሳዩ
ምልክቶች ሆነዋል። ጋዜጠኞቹ በርካታ ስጋት ውስጥ የሚገኙ፣ ማስፈራሪያ የሚደርሳቸው፣ አልፎ አልፎም አካላዊ
ጥቃት የሚፈጸምባቸው እና ፖለቲካዊ ይዘት ያለው የወንጀል ወይንም የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው ናቸው፡፡
የፍርድ ቤት ክርክራቸው ፍትሃዊ የፍርድ ሂደትን የሚጥሱ አሰራሮች የሚታዩበት ሲሆን ፍርድ ቤቶቹም
በያዟቸው ጉዳዮች ላይ የሚሰጧቸው ውሳኔዎች ገለልተኛ እንዳልሆኑ የሚያሳይ ነው።
በኢትዮጵያ የሚገኙት አብዛኛዎቹ የህትመት መገናኛ-ብዙሃን ከመግስት ጋር የቀረበ ትስስር አላቸው፤ በወሳኝ
ጉዳዮች ላይ ከመንግሰት የተለየ አቋም እምብዛም አያንጸባርቁም።የግል የህትመት መገናኛ-ብዙሃን በርካታ
ከቁጥጥር ጋር የተያያዙ ችግሮች ያጋጥማቸዋል እንዲሁም በደህንነት ሰራተኞች ተከታታይ ወከባ ይደርስባቸዋል፡፡
መንግስትን የሚተቹ የህትመት ውጤቶች በየጊዜው ይዘጋሉ፣ የበሰለ ትችት የሚያቀርቡ የህትመት ውጤቶችን
የሚያትሙ እና የሚያከፋፍሉ አሳታሚዎች እና አከፋፋዮችም ተዘግተዋል፡፡ የመንግስት ፖሊሲዎች ላይ ትችት
የሚሰነዝሩ ጋዜጠኞች እና የቤተሰብ አባሎቻቸው ጭምር የጥቃት፣ የመታሰር እና የገቢ ምንጫቸውን የማጣት
ዘላቂ ስጋት ላይ ይወድቃሉ፡፡ መንግስት አብዛኛውን የመገናኛ-ብዙሃን ተቆጣጥሮ የሚገኝ ሲሆን የቀሩት ጥቂት
የግል መገናኛ-ብዙሃንም በተለይ ለአሳሳቢ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ በሚሰጡት ሽፋን ራሳቸው ላይ ቅድመ ምርመራ
የሚያደርጉ ያደርጋሉ ይህም እንዘጋለን ከሚል ፍርሃት የመነጨ ነው፡፡
Wednesday, 21 January 2015
Ethiopia’s new expressway left 11dead
Horrific car accident on Ethiopia’s new expressway left 11dead
...............(Addis Standard) An early morning major car accident on Sunday January 18th on the newly opened Addis-Adama expressway has left eleven people dead on impact and nine people wounded. Five of the wounded have received life threatening wounds and are in critical conditions, an investigating officer told Addis Standard.
car accindet
car accident
The accident happened early at around 6:00 am when a driver of a Sinotruk coming from Adama, the capital of Oromia regional state 100 kms South of Addis Abeba, lost its track and derailed into the separation fence of the six lane expressway. The Sinotruck then hit a minivan carrying 16 people and was speeding from Addis Abeba to Adama, reducing the minivan to a quarter of its original size and killing the eleven people on board on impact.
“We have no idea how this could possibly happen,” an investigating officer on the spot told Addis Standard, “we are unable to know whether the driver of the truck is amongst the dead or has left the accident scene.” The driver and the assistant on the minivan were among the dead. Most of the passengers on the minivan were people going to celebrate the Epiphany celebrations of the Ethiopian Orthodox Church with their loved ones, the investigating office who wants to remain anonymous told us.
Due to massive construction works throughout the country, Ethiopia has seen a sharp increase in the numbers of the Chinese made Sinotruks. However, many Ethiopians complain of horrific car accidents caused by these tucks as most of them are operated by poorly trained drivers.
The 84.5 km Addis-Adama expressway, the first for the country, opened for traffic on Sep. 14th 2014. The six-lane expressway was built by China Communications and Construction Co. (CCCC) and financed by the government in Ethiopia and Exim Bank of china, which provided a US$800 million. The expressway has seven toll stations between Tulu Dimtu on the outskirts of Addis Abeba, and the last point in the western part of Adama...............source,-http://www.zehabesha.com/
Subscribe to:
Posts (Atom)