Wednesday, 17 December 2014
የዞን 9 ጦማርያን ፍርድ ቤት
የዞን 9 ጠበቃን ደብዳቤ ይዘናል
(ኢ.ኤም.ኤፍ) ከኦነግ እና ግንቦት 7 ጋር አብረው ሰርተዋል:: የሚል ክስ የተመሰረተባቸው ወጣት ጦማርያን ፍርድ ቤት በድጋሚ ቀርበው ነበር:: የቀረቡበት ምክንያት… የተጠቀሰው የወንጀል ዝርዝር እና አንቀጹ ተዛማጅ ባለመሆናቸው የጦማርያኑ ጠበቃ በክሱ ላይ ማስተካከያ እንዲደረግ ጠይቆ ነበር:: ጠበቃው ለፍርድ ቤት ካቀረቡት ደብዳቤ ውስጥ ገጽ 2 እና 3ትን ከዚህ ቀጥሎ አቅርበነዋል::
በፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ በሕቡዕ በመደራጀት፣ የወንጀል አድማ ስምምነት በማድረግ፣ በውጪ ኃይሎች በመደገፍና በማህበራዊ ድረ-ገፆች በመጠቀም እንዲሁም መንግሥት
አሸባሪ ብሎ ከሚጠራው ግንቦት 7 እና ኦነግ ጋር በመተባበር ሁከትና ብጥብጥን ሊያስነሱ ሲንቀሳቀሱ ነበር በሚል የሽብር ወንጀል ክስ በመሠረተባቸው በእነሶሊያን ሽመልስ የክስ መዝገብ ላይ አሁንም በድጋሚ መጥራት ያለባቸው ጉዳዮች አሉ በሚል; ከላይ በተገለጸው አይነት የተከሳሽ ጠበቆች አቤቱታቸው በፅሁፍ አቅርበዋል።
source,-http://ethioforum.org/amharic/
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment