Saturday, 6 December 2014

የሰላማዊ ሰልፉ ቅስቀሳ ቀጥሎ አምሽቷል

የሰላማዊ ሰልፉ ቅስቀሳ ቀጥሎ አምሽቷል የአዳር ሰላማዊ ሰልፉ ቅስቀሳ ምሽቱን ጭምር ተጠናክሮ እንደቀጠለ በሰማያዊ ፓርቲ በኩል የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አቶ ብርሃኑ እንደገለጹት የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዝብ በአገኘው አጋጣሚ ሁሉ የሰላማዊ ሰልፉን ቅስቀሳ እንዲያግዝ ባቀረበው ጥሪ መሰረት ህዝብ የቅስቀሳ ወረቀቶችን በማባዛት ዛሬ ህዳር 26/2007 ዓ.ም ምሽቱን ወረቀት ሲበትን ማምሸቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም መሰረት በአራት ኪሎ፣ ከስላሴ ጀምሮ በፒያሳና ማዕከላዊ ጀርባ በሚገኙ ሰፈሮች እንዲሁም በአዲሱ ገበያ ወረቀቶች እንደተበተኑ ገልጸዋል፡፡ ባለፉት ሁለት ቀናት የ9ኙ ፓርቲዎች ለቅስቀሳ ያዘጋጁት ስቲከር በተለያዩ የከተማይቱ አካባቢዎች እንደተለጠፉ መገለጹ ይታወቃል፡፡ “Freedom for Fair Election” rally on December 6-7, 2014 in Addis Ababa at Meskel Square (Abyot Adebabay) The 9 Ethiopian opposition coalition who called the rally says intense protest preparation is underway amid by police and security forces harassment. The 9 Ethiopian opposition coalition rally Semayawi Party office in Ethiopia's capital surrounded by police and kidnapped more members . .. source,.semayawi party

No comments:

Post a Comment